ዘኁልቁ 26:1-65

  • ሁለተኛው የእስራኤላውያን የሕዝብ ቆጠራ (1-65)

26  ከመቅሰፍቱ በኋላ+ ይሖዋ ሙሴንና የካህኑን የአሮንን ልጅ አልዓዛርን እንዲህ አላቸው፦  “ከመላው የእስራኤል ማኅበረሰብ መካከል ዕድሜያቸው 20 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆናቸውን በየአባቶቻቸው ቤት ቁጠሩ፤ በእስራኤል የጦር ሠራዊት ውስጥ ገብተው ማገልገል የሚችሉትን ሁሉ ቁጠሩ።”+  በመሆኑም ሙሴና ካህኑ አልዓዛር+ ከኢያሪኮ ማዶ+ በዮርዳኖስ አጠገብ በሚገኘው የሞዓብ በረሃማ ሜዳ+ ላይ ለሕዝቡ እንዲህ ሲሉ ተናገሩ፦  “ይሖዋ ሙሴን ባዘዘው መሠረት ዕድሜያቸው 20 ዓመትና ከዚያ በላይ የሆናቸውን ቁጠሩ።”+ ከግብፅ ምድር የወጡት የእስራኤል ልጆች የሚከተሉት ነበሩ፦  የእስራኤል የበኩር ልጅ ሮቤል፤+ የሮቤል ልጆች+ እነዚህ ነበሩ፦ ከሃኖክ የሃኖካውያን ቤተሰብ፣ ከፓሉ የፓላውያን ቤተሰብ፣  ከኤስሮን የኤስሮናውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከካርሚ የካርማውያን ቤተሰብ።  የሮቤላውያን ቤተሰቦች እነዚህ ነበሩ፤ ከእነሱም መካከል የተመዘገቡት 43,730 ነበሩ።+  የፓሉ ልጅ ኤልያብ ነበር።  የኤልያብ ልጆች ደግሞ ነሙኤል፣ ዳታን እና አቤሮን ነበሩ። እዚህ ላይ የተጠቀሱት ዳታን እና አቤሮን ቆሬና ግብረ አበሮቹ+ በይሖዋ ላይ ባመፁበት ወቅት+ ከእነሱ ጋር በማበር በሙሴና በአሮን ላይ የተነሱ የማኅበረሰቡ ተወካዮች ነበሩ።+ 10  ከዚያም ምድር አፏን ከፍታ ዋጠቻቸው። ቆሬም እሳት ወርዶ 250 ሰዎችን በበላ ጊዜ ከነግብረ አበሮቹ ሞተ።+ እነሱም የማስጠንቀቂያ ምሳሌ ሆኑ።+ 11  ይሁንና የቆሬ ልጆች አልሞቱም።+ 12  የስምዖን ልጆች+ በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፦ ከነሙኤል የነሙኤላውያን ቤተሰብ፣ ከያሚን የያሚናውያን ቤተሰብ፣ ከያኪን የያኪናውያን ቤተሰብ፣ 13  ከዛራ የዛራውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከሻኡል የሻኡላውያን ቤተሰብ። 14  የስምዖናውያን ቤተሰቦች እነዚህ ሲሆኑ እነሱም 22,200 ነበሩ።+ 15  የጋድ ልጆች+ በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፦ ከጸፎን የጸፎናውያን ቤተሰብ፣ ከሃጊ የሃጋውያን ቤተሰብ፣ ከሹኒ የሹናውያን ቤተሰብ፣ 16  ከኦዝኒ የኦዝናውያን ቤተሰብ፣ ከኤሪ የኤራውያን ቤተሰብ፣ 17  ከአሮድ የአሮዳውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከአርዔላይ የአርዔላውያን ቤተሰብ። 18  የጋድ ልጆች ቤተሰቦች እነዚህ ነበሩ፤ ከእነሱም መካከል የተመዘገቡት 40,500 ነበሩ።+ 19  የይሁዳ ልጆች+ ኤር እና ኦናን ነበሩ።+ ሆኖም ኤር እና ኦናን በከነአን ምድር ሞቱ።+ 20  የይሁዳ ልጆች በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፦ ከሴሎም+ የሴሎማውያን ቤተሰብ፣ ከፋሬስ+ የፋሬሳውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከዛራ+ የዛራውያን ቤተሰብ። 21  የፋሬስ ልጆች እነዚህ ነበሩ፦ ከኤስሮን+ የኤስሮናውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከሃሙል+ የሃሙላውያን ቤተሰብ። 22  የይሁዳ ቤተሰቦች እነዚህ ነበሩ፤ ከእነሱም መካከል የተመዘገቡት 76,500 ነበሩ።+ 23  የይሳኮር ልጆች+ በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፦ ከቶላ+ የቶላውያን ቤተሰብ፣ ከፑዋ የፑዋውያን ቤተሰብ፣ 24  ከያሹብ የያሹባውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከሺምሮን የሺምሮናውያን ቤተሰብ። 25  የይሳኮር ቤተሰቦች እነዚህ ነበሩ፤ ከእነሱም መካከል የተመዘገቡት 64,300 ነበሩ።+ 26  የዛብሎን ልጆች+ በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፦ ከሰሬድ የሰሬዳውያን ቤተሰብ፣ ከኤሎን የኤሎናውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከያህልኤል የያህልኤላውያን ቤተሰብ። 27  የዛብሎናውያን ቤተሰቦች እነዚህ ነበሩ፤ ከእነሱም መካከል የተመዘገቡት 60,500 ነበሩ።+ 28  የዮሴፍ ልጆች+ በየቤተሰባቸው ምናሴና ኤፍሬም ነበሩ።+ 29  የምናሴ ልጆች+ እነዚህ ነበሩ፦ ከማኪር+ የማኪራውያን ቤተሰብ፤ ማኪር ጊልያድን ወለደ፤+ ከጊልያድ የጊልያዳውያን ቤተሰብ። 30  የጊልያድ ልጆች እነዚህ ነበሩ፦ ከኢዔዝር የኢዔዝራውያን ቤተሰብ፣ ከሄሌቅ የሄሌቃውያን ቤተሰብ፣ 31  ከአስሪዔል የአስሪዔላውያን ቤተሰብ፣ ከሴኬም የሴኬማውያን ቤተሰብ፣ 32  ከሸሚዳ የሸሚዳውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከሄፌር የሄፌራውያን ቤተሰብ። 33  የሄፌር ልጅ ሰለጰአድ ሴቶች ልጆች ብቻ እንጂ ወንዶች ልጆች አልነበሩትም፤+ የሰለጰአድ ሴቶች ልጆች+ ስም ማህላ፣ ኖኅ፣ ሆግላ፣ ሚልካ እና ቲርጻ ነበር። 34  የምናሴ ቤተሰቦች እነዚህ ነበሩ፤ ከእነሱም መካከል የተመዘገቡት 52,700 ነበሩ።+ 35  የኤፍሬም ልጆች+ በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፦ ከሹተላ+ የሹተላውያን ቤተሰብ፣ ከቤኬር የቤኬራውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከታሃን የታሃናውያን ቤተሰብ። 36  የሹተላ ልጆች እነዚህ ነበሩ፦ ከኤራን የኤራናውያን ቤተሰብ። 37  የኤፍሬም ቤተሰቦች እነዚህ ነበሩ፤ ከእነሱም መካከል የተመዘገቡት 32,500 ነበሩ።+ የዮሴፍ ልጆች በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ። 38  የቢንያም ልጆች+ በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፦ ከቤላ+ የቤላውያን ቤተሰብ፣ ከአሽቤል የአሽቤላውያን ቤተሰብ፣ ከአሂራም የአሂራማውያን ቤተሰብ፣ 39  ከሼፉፋም የሼፉፋማውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከሁፋም የሁፋማውያን ቤተሰብ። 40  የቤላ ልጆች አርድ እና ንዕማን ነበሩ፤+ ከአርድ የአርዳውያን ቤተሰብ፣ ከንዕማን ደግሞ የንዕማናውያን ቤተሰብ። 41  የቢንያም ልጆች በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፤ ከእነሱም መካከል የተመዘገቡት 45,600 ነበሩ።+ 42  የዳን ልጆች+ በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፦ ከሹሃም የሹሃማውያን ቤተሰብ። የዳን ቤተሰቦች በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ። 43  ከሹሃማውያን ቤተሰቦች በሙሉ የተመዘገቡት 64,400 ነበሩ።+ 44  የአሴር ልጆች+ በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፦ ከይምናህ የይምናሃውያን ቤተሰብ፣ ከይሽዊ የይሽዋውያን ቤተሰብ፣ ከበሪአ የበሪአውያን ቤተሰብ፤ 45  ከበሪአ ልጆች፦ ከሄቤር የሄቤራውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከማልኪኤል የማልኪኤላውያን ቤተሰብ። 46  የአሴር ሴት ልጅ ስም ሴራህ ነበር። 47  የአሴር ልጆች ቤተሰቦች እነዚህ ነበሩ፤ ከእነሱም መካከል የተመዘገቡት 53,400 ነበሩ።+ 48  የንፍታሌም ልጆች+ በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፦ ከያህጽኤል የያህጽኤላውያን ቤተሰብ፣ ከጉኒ የጉናውያን ቤተሰብ፣ 49  ከየጼር የየጼራውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከሺሌም የሺሌማውያን ቤተሰብ። 50  የንፍታሌም ቤተሰቦች በየቤተሰባቸው እነዚህ ነበሩ፤ ከእነሱም መካከል የተመዘገቡት 45,400 ነበሩ።+ 51  ከእስራኤላውያን መካከል የተመዘገቡት በጠቅላላ 601,730 ነበሩ።+ 52  ከዚህ በኋላ ይሖዋ ሙሴን እንዲህ አለው፦ 53   “ምድሪቱ ለእነዚህ በስማቸው ዝርዝር መሠረት ርስት ሆና ትከፋፈል።+ 54  ተለቅ ላሉት ቡድኖች በዛ ያለ ውርሻ ትሰጣቸዋለህ፤ አነስ ላሉት ቡድኖች ደግሞ አነስ ያለ ውርሻ ትሰጣቸዋለህ።+ የእያንዳንዱ ቡድን ውርሻ በተመዘገቡት ሰዎች ብዛት ተመጣጥኖ መሰጠት አለበት። 55  ይሁን እንጂ ምድሪቱ መከፋፈል ያለባት በዕጣ ነው።+ ውርሻቸውንም ማግኘት ያለባቸው በአባቶቻቸው ነገዶች ስም መሠረት ነው። 56  እያንዳንዱ ውርሻ የሚወሰነው በዕጣ ሲሆን በኋላም ውርሻው እንደ ቡድኑ ትልቅነትና ትንሽነት ይከፋፈላል።” 57   ከሌዋውያኑ መካከል በየቤተሰባቸው የተመዘገቡት እነዚህ ነበሩ፦+ ከጌድሶን የጌድሶናውያን ቤተሰብ፣ ከቀአት+ የቀአታውያን ቤተሰብ እንዲሁም ከሜራሪ የሜራራውያን ቤተሰብ። 58  የሌዋውያን ቤተሰቦች እነዚህ ነበሩ፦ የሊብናውያን ቤተሰብ፣+ የኬብሮናውያን ቤተሰብ፣+ የማህላውያን ቤተሰብ፣+ የሙሻውያን ቤተሰብ+ እና የቆሬያውያን ቤተሰብ።+ ቀአት አምራምን ወለደ።+ 59  የአምራም ሚስት ስሟ ዮካቤድ ነበር፤+ እሷም የሌዊ ሚስት በግብፅ ለሌዊ የወለደችለት ናት። ዮካቤድም ለአምራም አሮንን፣ ሙሴንና እህታቸውን ሚርያምን ወለደችለት።+ 60  አሮንም ናዳብን፣ አቢሁን፣ አልዓዛርን እና ኢታምርን ወለደ።+ 61  ሆኖም ናዳብና አቢሁ በይሖዋ ፊት ያልተፈቀደ እሳት በማቅረባቸው ሞቱ።+ 62  አንድ ወርና ከዚያ በላይ ሆኗቸው የተመዘገቡት ወንዶች በአጠቃላይ 23,000 ነበሩ።+ እነዚህ በእስራኤላውያን መካከል ርስት ስለማይሰጣቸው+ ከእስራኤላውያን ጋር አልተመዘገቡም።+ 63  እነዚህም ሙሴና ካህኑ አልዓዛር ከኢያሪኮ ማዶ በዮርዳኖስ አጠገብ በሚገኘው የሞዓብ በረሃማ ሜዳ ላይ እስራኤላውያንን በመዘገቡበት ወቅት የመዘገቧቸው ናቸው። 64  ሆኖም ከእነዚህ መካከል ሙሴና ካህኑ አሮን እስራኤላውያንን በሲና ምድረ በዳ በቆጠሩበት ወቅት ተመዝግቦ የነበረ አንድም ሰው አልነበረም።+ 65  ምክንያቱም ይሖዋ እነሱን በተመለከተ “በእርግጥ በምድረ በዳው ላይ ያልቃሉ”+ በማለት ተናግሮ ነበር። በመሆኑም ከየፎኒ ልጅ ከካሌብና ከነዌ ልጅ ከኢያሱ በስተቀር አንድም የተረፈ ሰው አልነበረም።+

የግርጌ ማስታወሻዎች