በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የመሳፍንት መጽሐፍ

ምዕራፎች

1 2 3 4 5 6 7 8 9 10 11 12 13 14 15 16 17 18 19 20 21

የመጽሐፉ ይዘት

  • 1

    • ይሁዳና ስምዖን ድል አድርገው የያዟቸው ግዛቶች (1-20)

    • ኢያቡሳውያን በኢየሩሳሌም መኖራቸውን ቀጠሉ (21)

    • ዮሴፍ ቤቴልን ያዘ (22-26)

    • ከነአናውያን ሙሉ በሙሉ ከምድሪቱ አልተባረሩም (27-36)

  • 2

    • የይሖዋ መልአክ የሰጠው ማስጠንቀቂያ (1-5)

    • ኢያሱ ሞተ (6-10)

    • እስራኤልን የሚታደጉ መሳፍንት ተነሱ (11-23)

  • 3

    • ይሖዋ እስራኤላውያንን ፈተናቸው (1-6)

    • ኦትኒኤል፣ የመጀመሪያው መስፍን (7-11)

    • መስፍኑ ኤሁድ ወፍራም የሆነውን ንጉሥ ኤግሎንን ገደለው (12-30)

    • መስፍኑ ሻምጋር (31)

  • 4

    • ከነአናዊው ንጉሥ ያቢን እስራኤላውያንን ጨቆናቸው (1-3)

    • ነቢዪቱ ዲቦራና መስፍኑ ባርቅ (4-16)

    • ኢያዔል የሠራዊት አለቃ የሆነውን ሲሳራን ገደለችው (17-24)

  • 5

    • የዲቦራና የባርቅ የድል መዝሙር (1-31)

      • ከዋክብት ከሲሳራ ጋር ተዋጉ (20)

      • የቂሾን ወንዝ ጠራርጎ ወሰዳቸው (21)

      • ይሖዋን የሚወዱ እንደ ፀሐይ ይሁኑ (31)

  • 6

    • ምድያማውያን እስራኤላውያንን ጨቆኗቸው (1-10)

    • አንድ መልአክ መስፍኑን ጌድዮንን እንደሚረዳው ቃል ገባለት (11-24)

    • ጌድዮን የባአልን መሠዊያ አፈራረሰ (25-32)

    • የአምላክ መንፈስ በጌድዮን ላይ ወረደ (33-35)

    • ጌድዮን በተባዘተው የበግ ፀጉር ያደረገው ሙከራ (36-40)

  • 7

    • ጌድዮንና 300ዎቹ ሰዎች (1-8)

    • የጌድዮን ሠራዊት ምድያማውያንን ድል አደረገ (9-25)

      • “የይሖዋና የጌድዮን ሰይፍ!” (20)

      • በምድያማውያን የጦር ሰፈር የተከሰተው ግራ መጋባት (21, 22)

  • 8

    • ኤፍሬማውያን ከጌድዮን ጋር ተጣሉ (1-3)

    • ምድያማውያን ነገሥታትን አሳደው በመያዝ ገደሏቸው (4-21)

    • ጌድዮን ሊያነግሡት ሲሉ እንቢ አለ (22-27)

    • የጌድዮን ሕይወት (28-35)

  • 9

    • አቢሜሌክ በሴኬም ነገሠ (1-6)

    • የኢዮዓታም ምሳሌ (7-21)

    • የአቢሜሌክ ጨቋኝ አገዛዝ (22-33)

    • አቢሜሌክ በሴኬም ላይ ጥቃት ሰነዘረ (34-49)

    • አንዲት ሴት በአቢሜሌክ ላይ የወፍጮ መጅ ጣለችበት፤ እሱም ሞተ (50-57)

  • 10

    • መሳፍንቱ ቶላና ያኢር (1-5)

    • እስራኤላውያን ዓመፁ፤ በኋላም ንስሐ ገቡ (6-16)

    • አሞናውያን እስራኤላውያንን ለመውጋት ተሰበሰቡ (17, 18)

  • 11

    • መስፍኑ ዮፍታሔ ከአባቱ ቤት ተባረረ፤ በኋላም መሪ ሆነ (1-11)

    • ዮፍታሔ ለአሞናውያን ንጉሥ መልእክት ላከ (12-28)

    • የዮፍታሔ ስእለትና ሴት ልጁ (29-40)

      • የዮፍታሔ ልጅ ሳታገባ ኖረች (38-40)

  • 12

    • ከኤፍሬማውያን ጋር የተፈጠረ ግጭት (1-7)

      • “እስቲ ሺቦሌት በል” (6)

    • መሳፍንቱ ኢብጻን፣ ኤሎን እና አብዶን (8-15)

  • 13

    • አንድ መልአክ ማኑሄንና ሚስቱን አነጋገራቸው (1-23)

    • ሳምሶን ተወለደ (24, 25)

  • 14

    • መስፍኑ ሳምሶን ፍልስጤማዊት ሴት ማግባት ፈለገ (1-4)

    • ሳምሶን በይሖዋ መንፈስ እርዳታ አንበሳ ገደለ (5-9)

    • የሳምሶን እንቆቅልሽ (10-19)

    • የሳምሶን ሚስት ለሌላ ሰው ተዳረች (20)

  • 15

    • ሳምሶን ፍልስጤማውያንን ተበቀለ (1-20)

  • 16

    • ሳምሶን ወደ ጋዛ ሄደ (1-3)

    • ሳምሶንና ደሊላ (4-22)

    • የሳምሶን የበቀል እርምጃና ሞት (23-31)

  • 17

    • የሚክያስ ጣዖታትና ካህኑ (1-13)

  • 18

    • ዳናውያን ተጨማሪ ርስት ፈለጉ (1-31)

      • ዳናውያን የሚክያስን ጣዖታትና ካህን ወሰዱ (14-20)

      • ላይሽን ያዟት፤ ዳን ብለው ጠሯት (27-29)

      • ዳን ውስጥ የጣዖት አምልኮ ተስፋፋ (30, 31)

  • 19

    • ቢንያማውያን በጊብዓ የፈጸሙት የፆታ ጥቃት (1-30)

  • 20

    • እስራኤላውያን ከቢንያማውያን ጋር ተዋጉ (1-48)

  • 21

    • የቢንያም ነገድ ከመጥፋት ተረፈ (1-25)