በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ትምህርት 1

የይሖዋ ምሥክሮች ምን ዓይነት ሰዎች ናቸው?

የይሖዋ ምሥክሮች ምን ዓይነት ሰዎች ናቸው?

ዴንማርክ

ታይዋን

ቬኔዙዌላ

ሕንድ

የምታውቃቸው የይሖዋ ምሥክሮች አሉ? ምናልባትም ጎረቤቶችህ፣ የሥራ ባልደረቦችህ ወይም አብረውህ የሚማሩት ልጆች የይሖዋ ምሥክሮች ይሆናሉ። ወይም ከእነሱ ጋር መጽሐፍ ቅዱሳዊ ውይይት አድርገህ ታውቅ ይሆናል። ይሁን እንጂ እኛ የይሖዋ ምሥክሮች ምን ዓይነት ሰዎች ነን? ስለ እምነታችን ለሰዎች የምንናገረውስ ለምንድን ነው?

እንደ ማንኛውም ሰው ነን። የተለያየ አስተዳደግና ማኅበራዊ ሁኔታ ያለን ሰዎች ነን። አንዳንዶቻችን የይሖዋ ምሥክር ከመሆናችን በፊት የሌላ ሃይማኖት አባላት ነበርን፤ ሌሎቻችን ደግሞ በአምላክ የማናምን ሰዎች ነበርን። የይሖዋ ምሥክር ከመሆናችን በፊት ግን ሁላችንም ጊዜ ወስደን የመጽሐፍ ቅዱስን ትምህርቶች በጥንቃቄ መርምረናል። (የሐዋርያት ሥራ 17:11) ከዚያም የተማርነውን ነገር ስላመንንበት ይሖዋ አምላክን ለማምለክ በግለሰብ ደረጃ ውሳኔ አደረግን።

መጽሐፍ ቅዱስን ማጥናታችን ጠቅሞናል። እንደ ማንኛውም ሰው ሁሉ እኛም ከተለያዩ ችግሮችና ከራሳችን ድክመት ጋር መታገል ያስፈልገናል። ይሁን እንጂ በዕለታዊ ሕይወታችን የመጽሐፍ ቅዱስን መመሪያዎች ተግባራዊ ለማድረግ ስለምንጥር በሕይወታችን ውስጥ ጉልህ ለውጥ መመልከት ችለናል። (መዝሙር 128:1, 2) ከመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተማርናቸውን መልካም ነገሮች ለሌሎች የምናካፍልበት አንዱ ምክንያት ይህ ነው።

የአምላክን መመሪያዎች አክብረን እንኖራለን። በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ የሚገኙት እነዚህ መመሪያዎች በአካልም ሆነ በአስተሳሰብ ጤናማ እንድንሆን የሚረዱን ከመሆኑም ሌላ ለሰዎች አክብሮት እንዲኖረን እንዲሁም እንደ ሐቀኝነትና ደግነት ያሉትን ጥሩ ባሕርያት እንድናፈራ ያስችሉናል። የአምላክ መመሪያዎች፣ ዜጎች ጤናማና ጠቃሚ የማኅበረሰቡ አባላት እንዲሆኑ አስተዋጽኦ ያበረክታሉ፤ አልፎ ተርፎም ቤተሰቦች አንድነትና ጥሩ ሥነ ምግባር እንዲኖራቸው እገዛ ያደርጋሉ። “አምላክ እንደማያዳላ” ስለምናምን በዘርና በፖለቲካ ያልተከፋፈለና ዓለም አቀፋዊ የሆነ መንፈሳዊ የወንድማማች ማኅበር አለን። በዚህም የተነሳ፣ እንደ ማንኛውም ሰው ብንሆንም ልዩ ሕዝብ መሆን ችለናል።—የሐዋርያት ሥራ 4:13፤ 10:34, 35

  • የይሖዋ ምሥክሮችን ከሌሎች ሰዎች ጋር የሚያመሳስላቸው ምንድን ነው?

  • የይሖዋ ምሥክሮች መጽሐፍ ቅዱስን በማጥናታቸው የትኞቹን መመሪያዎች ማወቅ ችለዋል?