በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ትምህርት 7

ስብሰባዎቻችን ምን ይመስላሉ?

ስብሰባዎቻችን ምን ይመስላሉ?

ኒው ዚላንድ

ጃፓን

ኡጋንዳ

ሊቱዌኒያ

የጥንቶቹ ክርስቲያኖች በስብሰባዎች ላይ ይዘምሩ፣ ይጸልዩ እንዲሁም ቅዱሳን መጻሕፍትን እያነበቡ ይወያዩ ነበር፤ የስብሰባው ዋነኛ ገጽታዎች እነዚህ ሲሆኑ ከዚህ ውጭ ለየት ያለ የአምልኮ ሥርዓት አያካሂዱም ነበር። (1 ቆሮንቶስ 14:26) በእኛ ስብሰባዎች ላይ የሚከናወነው ሁኔታም ተመሳሳይ ነው።

ትምህርቱ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመሠረተና ተግባራዊ ሊሆን የሚችል ነው። በሳምንቱ መጨረሻ ላይ በእያንዳንዱ ጉባኤ ውስጥ 30 ደቂቃ የሚወስድ በመጽሐፍ ቅዱስ ላይ የተመሠረተ ንግግር የሚቀርብ ሲሆን ንግግሩም ቅዱሳን መጻሕፍት ከሕይወታችንና ከምንኖርበት ዘመን ጋር በተያያዘ በሚሰጡት መመሪያ ላይ ያተኮረ ነው። ጥቅሶች ሲነበቡ ሁላችንም መጽሐፍ ቅዱሳችንን አውጥተን እንድንከታተል እንበረታታለን። ከንግግሩ በኋላ አንድ ሰዓት የሚወስድ “የመጠበቂያ ግንብ” ጥናት ይደረጋል፤ በመጠበቂያ ግንብ የጥናት እትም ላይ በወጣ አንድ ርዕስ ላይ በሚደረገው በዚህ ውይይት ሁሉም የጉባኤው አባላት እንዲካፈሉ ይጋበዛሉ። ይህ ውይይት የመጽሐፍ ቅዱስን መመሪያዎች በሕይወታችን ውስጥ ሥራ ላይ እንድናውል ይረዳናል። በምድር ዙሪያ በሚገኙት ከ110,000 የሚበልጡ ጉባኤዎች ውስጥ የሚጠናው ርዕስ ተመሳሳይ ነው።

የማስተማር ችሎታችንን ለማሻሻል እርዳታ እናገኛለን። በሳምንቱ መሃል ደግሞ ሦስት ክፍሎች ያሉት ስብሰባ እናደርጋለን፤ ይህ ስብሰባ ክርስቲያናዊ ሕይወታችንና አገልግሎታችን በመባል ይጠራል፤ ትምህርቱ የተመሠረተው በየወሩ በሚወጣው የክርስቲያናዊ ሕይወትና አገልግሎት ስብሰባ አስተዋጽኦ ላይ ነው። የዚህ ስብሰባ የመጀመሪያ ክፍል “ከአምላክ ቃል የሚገኝ ውድ ሀብት” የሚባል ሲሆን የጉባኤው አባላት አስቀድመው ያነበቡት የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍል ይብራራል። ቀጥሎ የሚቀርበው “በአገልግሎት ውጤታማ ለመሆን ተጣጣር” የተባለው ክፍል ደግሞ ከሰዎች ጋር መጽሐፍ ቅዱስን እንዴት መወያየት እንደምንችል የሚያሳዩ ሠርቶ ማሳያዎችን ያካተተ ነው። ምክር ሰጪው የንባብና የማስተማር ችሎታችንን ለማሻሻል የሚረዱ ነጥቦችን ይነግረናል። (1 ጢሞቴዎስ 4:​13) “ክርስቲያናዊ ሕይወት” የተባለው የመጨረሻው ክፍል፣ የመጽሐፍ ቅዱስን መሠረታዊ ሥርዓቶች በዕለት ተዕለት ሕይወታችን ተግባራዊ ማድረግ የምንችልባቸውን መንገዶች ይጠቁመናል። በዚህ ክፍል ውስጥ በጥያቄና መልስ የሚካሄድ ውይይት የሚካተት ሲሆን ይህም ስለ መጽሐፍ ቅዱስ ያለንን ግንዛቤ ያሰፋልናል።

በስብሰባዎቻችን ላይ በምትገኝበት ጊዜ በስብሰባው ላይ በሚቀርበው መጽሐፍ ቅዱሳዊ ትምህርት መደነቅህ አይቀርም።—ኢሳይያስ 54:13

  • የይሖዋ ምሥክሮች በሚያደርጓቸው ስብሰባዎች ላይ ምን ትምህርቶች ይቀርባሉ?

  • ከሳምንታዊ ስብሰባዎቻችን በየትኛው ላይ መገኘት ትፈልጋለህ?