በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ትምህርት 17

የወረዳ የበላይ ተመልካቾች የሚጠቅሙን እንዴት ነው?

የወረዳ የበላይ ተመልካቾች የሚጠቅሙን እንዴት ነው?

ማላዊ

የስምሪት ስብሰባ

የመስክ አገልግሎት

የሽማግሌዎች ስብሰባ

የክርስቲያን ግሪክኛ ቅዱሳን መጻሕፍት ስለ በርናባስና ስለ ሐዋርያው ጳውሎስ በተደጋጋሚ ይጠቅሳሉ። እነዚህ ወንድሞች ተጓዥ የበላይ ተመልካቾች በመሆን የጥንቶቹን ጉባኤዎች ይጎበኙ ነበር። ይህን ያደርጉ የነበረው ለምንድን ነው? ስለ መንፈሳዊ ወንድሞቻቸው ደህንነት ከልባቸው ያስቡ ስለነበር ነው። ጳውሎስ “ወንድሞች በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኙ ለማወቅ” ሲል ‘ተመልሶ ሊጠይቃቸው’ እንደሚፈልግ ተናግሯል። እነሱን ሄዶ ለማበረታታት በመቶዎች የሚቆጠሩ ኪሎ ሜትሮች ለመጓዝ ፈቃደኛ ነበር። (የሐዋርያት ሥራ 15:36) ዛሬም ያሉት ተጓዥ የበላይ ተመልካቾች ተመሳሳይ ስሜት አላቸው።

ማበረታቻ ይሰጡናል። እያንዳንዱ የወረዳ የበላይ ተመልካች ወደ 20 ገደማ የሚሆኑ ጉባኤዎችን በዓመት ሁለት ጊዜ የሚጎበኝ ሲሆን በእያንዳንዱ ጉብኝት ወቅት ከጉባኤው ጋር ለአንድ ሳምንት ይቆያል። ከእነዚህ ወንድሞችና ያገቡ ከሆኑ ደግሞ ከሚስቶቻቸው ተሞክሮም ብዙ ጥቅም ልናገኝ እንችላለን። የወረዳ የበላይ ተመልካቾችም ሆኑ ሚስቶቻቸው፣ ወጣት ሽማግሌ ሳይሉ ከሁላችንም ጋር ለመተዋወቅ ጥረት ያደርጋሉ፤ በተጨማሪም አብረውን በመስክ አገልግሎት ለመሰማራትና የመጽሐፍ ቅዱስ ጥናቶቻችንን ለማስጠናት ይፈልጋሉ። እነዚህ የበላይ ተመልካቾች ከሽማግሌዎች ጋር ሆነው እረኝነት ያደርጋሉ፤ እንዲሁም በጉባኤና በትላልቅ ስብሰባዎች ላይ የሚያበረታቱና እምነትን የሚያጠናክሩ ንግግሮች ያቀርባሉ።—የሐዋርያት ሥራ 15:35

ለሁሉም አሳቢነት ያሳያሉ። የወረዳ የበላይ ተመልካቾች የጉባኤዎች መንፈሳዊ ሁኔታ ከልብ ያሳስባቸዋል። ስለ ጉባኤው እንቅስቃሴ ለመወያየት ከሽማግሌዎችና ከጉባኤ አገልጋዮች ጋር ስብሰባ የሚያደርጉ ሲሆን ለእነዚህ ወንድሞች ኃላፊነቶቻቸውን ከሚወጡበት መንገድ ጋር በተያያዘ ጠቃሚ ምክር ይለግሷቸዋል። አቅኚዎች በአገልግሎታቸው ውጤታማ መሆን እንዲችሉ ይረዷቸዋል፤ እንዲሁም ከአዳዲሶች ጋር መጨዋወትና ስላደረጉት መንፈሳዊ እድገት መስማት በጣም ያስደስታቸዋል። ራሳቸውን በፈቃደኝነት የሚያቀርቡት እነዚህ ወንድሞች በሙሉ ‘ለእኛ ጥቅም አብረውን የሚሠሩ ባልደረቦቻችን’ ናቸው። (2 ቆሮንቶስ 8:23) በመሆኑም እምነታቸውንና ለአምላክ ያደሩ በመሆን ረገድ የሚተዉትን ምሳሌ መከተል አለብን።—ዕብራውያን 13:7

  • የወረዳ የበላይ ተመልካቾች ጉባኤዎችን የሚጎበኙበት ዓላማ ምንድን ነው?

  • ከጉብኝታቸው ጥቅም ልታገኝ የምትችለው እንዴት ነው?