በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ትምህርት 20

በዛሬው ጊዜ የበላይ አካሉ ሥራውን የሚያከናውነው እንዴት ነው?

በዛሬው ጊዜ የበላይ አካሉ ሥራውን የሚያከናውነው እንዴት ነው?

የመጀመሪያው መቶ ዘመን የበላይ አካል

የበላይ አካሉ ደብዳቤ ሲነበብ

በአንደኛው መቶ ዘመን በኢየሩሳሌም የሚገኙ ‘ሐዋርያትንና ሽማግሌዎችን’ ያቀፈ አንድ ትንሽ ቡድን መላውን የቅቡዓን ክርስቲያኖች ጉባኤ ወክሎ ትልቅ ቦታ የሚሰጣቸው ውሳኔዎችን የሚያስተላልፍ የበላይ አካል ሆኖ አገልግሏል። (የሐዋርያት ሥራ 15:2) የዚህ የበላይ አካል አባላት በአንድ ድምፅ ውሳኔ ማስተላለፍ የቻሉት በቅዱሳን መጻሕፍት ላይ ስለተወያዩና የመንፈስ ቅዱስን አመራር ስለተከተሉ ነበር። (የሐዋርያት ሥራ 15:25) ዛሬም ያለው የበላይ አካል የእነሱን ምሳሌ ይከተላል።

አምላክ ፈቃዱን ለማድረግ በበላይ አካሉ ይጠቀማል። የበላይ አካል አባላት ሆነው የሚያገለግሉት ቅቡዓን ወንድሞች ለአምላክ ቃል ትልቅ ቦታ የሚሰጡ ሲሆን ከመንፈሳዊ ነገሮችም ሆነ ከሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የረጅም ጊዜ ልምድ ያካበቱ ናቸው። እነዚህ ወንድሞች ዓለም አቀፉን የወንድማማች ማኅበር ስለሚመለከቱ ጉዳዮች ለመወያየት በየሳምንቱ ስብሰባ ያደርጋሉ። በአንደኛው መቶ ዘመን ይደረግ እንደነበረው ሁሉ መጽሐፍ ቅዱስን መሠረት ያደረጉ መመሪያዎች የሚተላለፉት በደብዳቤዎች፣ በተጓዥ የበላይ ተመልካቾችና በሌሎች ወንድሞች አማካኝነት ነው። ይህም የአምላክ ሕዝቦች አስተሳሰባቸውም ሆነ ተግባራቸው አንድ ዓይነት እንዲሆን አስችሏል። (የሐዋርያት ሥራ 16:4, 5) የበላይ አካሉ የመንፈሳዊ ምግቦችን ዝግጅት እንዲሁም ወንድሞች ለኃላፊነት ቦታ የሚሾሙበትን ሁኔታ በበላይነት ይከታተላል፤ በተጨማሪም ለመንግሥቱ ስብከት ሥራ ቅድሚያ እንድንሰጥ ያበረታታናል።

የበላይ አካሉ የአምላክን መንፈስ አመራር ይከተላል። የበላይ አካሉ መመሪያ ለማግኘት የጽንፈ ዓለሙ ሉዓላዊ ገዢ ወደሆነው ወደ ይሖዋና የጉባኤው ራስ ወደሆነው ወደ ኢየሱስ ዘወር ይላል። (1 ቆሮንቶስ 11:3፤ ኤፌሶን 5:23) የበላይ አካሉ አባላት ራሳቸውን የአምላክ ሕዝቦች መሪዎች እንደሆኑ አድርገው አይቆጥሩም። እነሱም ሆኑ የቀሩት ቅቡዓን ክርስቲያኖች “ምንጊዜም በጉ [ኢየሱስ] በሄደበት ሁሉ ይከተሉታል።” (ራእይ 14:4) የበላይ አካሉ አባላት ስለ እነሱ ለምናቀርበው ጸሎት አመስጋኞች ናቸው።

  • በመጀመሪያው መቶ ዘመን የበላይ አካል አባላት የነበሩት እነማን ናቸው?

  • በዛሬው ጊዜ የበላይ አካሉ የአምላክን አመራር ለማግኘት ምን ያደርጋል?