በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ትምህርት 26

የስብሰባ አዳራሻችንን በመንከባከብ ረገድ አስተዋጽኦ ማድረግ የምንችለው እንዴት ነው?

የስብሰባ አዳራሻችንን በመንከባከብ ረገድ አስተዋጽኦ ማድረግ የምንችለው እንዴት ነው?

ኢስቶንያ

ዚምባብዌ

ሞንጎሊያ

ፖርቶ ሪኮ

እያንዳንዱ የይሖዋ ምሥክሮች የስብሰባ አዳራሽ የአምላክ ቅዱስ ስም ይጠራበታል። በመሆኑም የሕንፃውን ንጽሕናና ውበት በመጠበቁ እንዲሁም አዳራሹን በማደሱ ሥራ መካፈልን እንደ ትልቅ መብት የምንመለከተው ከመሆኑም ሌላ ቅዱስ የሆነው አምልኳችን ክፍል እንደሆነ አድርገን እንቆጥረዋለን። በዚህ ሥራ ሁሉም ሰው መካፈል ይችላል።

ከስብሰባዎች በኋላ በሚደረገው መጠነኛ ጽዳት ተካፈል። ወንድሞችና እህቶች ከእያንዳንዱ ስብሰባ በኋላ በስብሰባ አዳራሹ ውስጥ ቀለል ያለ ጽዳት ማከናወን ያስደስታቸዋል። በሳምንት አንድ ጊዜ ደግሞ ይበልጥ ሰፋ ያለ ጽዳት ይደረጋል። አንድ ሽማግሌ ወይም የጉባኤ አገልጋይ ጽዳቱ የሚያካትታቸው ነገሮች የተጻፉበትን ዝርዝር በመያዝ ሥራውን ያስተባብራል። ወንድሞችና እህቶች እንደ አስፈላጊነቱ ወለሉን ይጠርጋሉ፣ ይወለውላሉ፣ አቧራ ያነሳሉ፣ ወንበሮችን ያስተካክላሉ፣ መጸዳጃ ቤቶችን ያጸዳሉ፣ መስተዋቶችን ይወለውላሉ፣ ቆሻሻ ይደፋሉ፣ ግቢውን ያጸዳሉ እንዲሁም አትክልቶችን ይንከባከባሉ። ቢያንስ በዓመት አንድ ጊዜ አዳራሹ የተሟላ ጽዳት ይደረግለታል። ልጆቻችንም በአንዳንድ ሥራዎች እንዲካፈሉ በማድረግ ለአምልኮ ቦታችን አክብሮት እንዲኖራቸው ልናሠለጥናቸው እንችላለን።—መክብብ 5:1

ለአዳራሹ ጥገና በሚደረግበት ጊዜ እገዛ አድርግ። በየዓመቱ የስብሰባ አዳራሹ ውስጡም ሆነ ውጭው በምን ሁኔታ ላይ እንደሚገኝ በደንብ ይገመገማል። ይህን መሠረት በማድረግ በየጊዜው የጥገና ሥራ ይከናወናል፤ ይህም አዳራሹ ምንጊዜም በጥሩ ሁኔታ እንዲገኝ ስለሚያደርግ አላስፈላጊ ከሆነ ወጪ ያድናል። (2 ዜና መዋዕል 24:13፤ 34:10) የስብሰባ አዳራሻችን ንጹሕና በተገቢው ሁኔታ የተያዘ ከሆነ አምላካችንን ለማምለክ የሚመጥን ይሆናል። በዚህ ሥራ በመካፈል ለይሖዋ ያለንን ፍቅርና ለአምልኮ ቦታችን ያለንን አክብሮት እናሳያለን። (መዝሙር 122:1) አዳራሻችንን ጥሩ አድርገን መያዛችን የአካባቢው ሰዎች ስለ እኛ በጎ አመለካከት እንዲኖራቸውም ያደርጋል።—2 ቆሮንቶስ 6:3

  • የአምልኮ ቦታችንን ችላ ማለት የማይገባን ለምንድን ነው?

  • የስብሰባ አዳራሹን ንጽሕና ለመጠበቅ ምን ዝግጅቶች ተደርገዋል?