በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ትምህርት 5

የኖኅ መርከብ

የኖኅ መርከብ

ከጊዜ በኋላ በምድር ላይ የሚኖሩት ሰዎች ቁጥር እየጨመረ መጣ። አብዛኞቹ ሰዎች ክፉዎች ነበሩ። በሰማይ ይኖሩ የነበሩ አንዳንድ መላእክትም እንኳ ክፉዎች ሆኑ። በሰማይ ያለውን መኖሪያቸውን ትተው ወደ ምድር ወረዱ። ለምን እንዲህ እንዳደረጉ ታውቃለህ? እንደ ሰው ሆነው ሴቶችን ማግባት ስለፈለጉ ነው።

መላእክቱና ሴቶቹ ተጋብተው ልጆች ወለዱ። እነዚህ ልጆች ሲያድጉ በጣም ጠንካራና ጉልበተኛ ሆኑ። ሰዎችንም መጉዳት ጀመሩ። ይሖዋ ይህ ሁኔታ እንዲቀጥል አልፈለገም። ስለሆነም ክፉ ሰዎችን በውኃ ለማጥፋት ወሰነ።

ሆኖም ከእነዚህ ሰዎች የተለየ አንድ ሰው ነበር። ይህ ሰው ኖኅ ይባላል፤ እሱም ይሖዋን በጣም ይወድ ነበር። ኖኅ ሚስትና ሦስት ወንዶች ልጆች ነበሩት፤ የልጆቹ ስም ሴም፣ ካምና ያፌት ሲሆን ሁሉም ሚስት ነበራቸው። ይሖዋ ኖኅን፣ እሱና ቤተሰቡ ከጥፋት ውኃው መትረፍ እንዲችሉ ትልቅ መርከብ እንዲሠራ ነገረው። ኖኅ የሠራው መርከብ በውኃ ላይ መንሳፈፍ የሚችል ትልቅ ሣጥን ይመስል ነበር። ይሖዋ ኖኅን እንስሳትም መትረፍ እንዲችሉ ወደ መርከቡ እንዲያስገባቸው ነገረው።

ኖኅ ወዲያውኑ መርከቡን መሥራት ጀመረ። ኖኅና ቤተሰቡ መርከቡን ሠርተው ለመጨረስ 50 ዓመት አካባቢ ፈጅቶባቸዋል። መርከቡን ልክ ይሖዋ እንዳዘዛቸው አድርገው ሠሩ። ኖኅ መርከቡን እየሠራ በነበረበት ጊዜ ሰዎች ከጥፋት ውኃው እንዲድኑ ያስጠነቅቅ ነበር። ግን ማንም አልሰማውም።

በመጨረሻም ወደ መርከቡ የሚገቡበት ጊዜ ደረሰ። እስቲ ቀጥሎ ምን እንደሆነ እንመልከት

“በኖኅ ዘመን እንደነበረው ሁሉ የሰው ልጅ መገኘትም እንደዚሁ ይሆናል።”—ማቴዎስ 24:37