በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የክፍል 2 ማስተዋወቂያ

የክፍል 2 ማስተዋወቂያ

ይሖዋ በጥንት ዘመን የነበረውን ዓለም በውኃ ያጠፋው ለምንድን ነው? በሰው ልጅ ታሪክ መጀመሪያ ላይ ሰይጣን በይሖዋ ላይ ዓመፀ። እንደ አዳም፣ ሔዋንና ቃየን ያሉ ሰዎች ከሰይጣን ጎን ለመሰለፍ መረጡ። እንደ አቤልና ኖኅ ያሉ ጥቂት ሰዎች ደግሞ ከይሖዋ ጎን ለመሰለፍ መረጡ። አብዛኞቹ ሰዎች በጣም መጥፎ ሆነው ስለነበር ይሖዋ ያንን ክፉ ዓለም አጠፋው። ይህ ክፍል፣ ይሖዋ ከእሱ ጎን አለዚያም ከሰይጣን ጎን ለመሰለፍ የምናደርገውን ምርጫ እንደሚመለከት ይገልጻል። ከዚህም ሌላ ይሖዋ በአሁኑ ጊዜም ቢሆን ክፋት መልካም የሆነውን ነገር እንዲያሸንፍ እንደማይፈቅድ ያብራራል።

በዚህ ክፍል ውስጥ

ትምህርት 3

አዳምና ሔዋን አምላክን ሳይታዘዙ ቀሩ

በኤደን የአትክልት ስፍራ ውስጥ የነበረው አንድ ዛፍ ከሌሎቹ የተለየ ነበር የምንለው ለምንድን ነው? ሔዋን የዚህን ዛፍ ፍሬ የበላችው ለምንድን ነው?

ትምህርት 4

ቃየን ተናዶ ወንድሙን ገደለው

አምላክ የአቤልን መባ ሲቀበል የቃየንን ግን አልተቀበለም። ቃየን ይህን ሲያውቅ በጣም ስለተናደደ መጥፎ ነገር አደረገ።

ትምህርት 5

የኖኅ መርከብ

ክፉ መላእክት በምድር ላይ የሚኖሩ ሴቶችን አግብተው ግዙፍና ጉልበተኛ የሆኑ ልጆችን ወለዱ። በሁሉም ቦታ ዓመፅ ተስፋፍቶ ነበር። ኖኅ ግን ከሌሎቹ የተለየ ነበር፤ አምላክን ይወድና ይታዘዝ ነበር።

ትምህርት 6

ስምንት ሰዎች ከጥፋት ውኃው ተረፉ

አምላክ በኖኅ ዘመን የነበረውን ዓለም ለማጥፋት 40 ቀንና 40 ሌሊት እንዲዘንብ አደረገ። ኖኅና ቤተሰቡ ከአንድ ዓመት በላይ በመርከቡ ውስጥ ቆዩ። በመጨረሻም መውጣት ቻሉ።