በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የክፍል 4 ማስተዋወቂያ

የክፍል 4 ማስተዋወቂያ

በዚህ ክፍል ላይ የዮሴፍን፣ የኢዮብን፣ የሙሴንና የእስራኤላውያንን ታሪክ እንመለከታለን። ዲያብሎስ በእነዚህ ሰዎች ላይ ብዙ መከራ አድርሶባቸዋል። አንዳንዶቹ የፍትሕ መጓደል ደርሶባቸዋል፣ ታስረዋል፣ ባሪያ ሆነዋል እንዲሁም የሚወዱትን ሰው በሞት አጥተዋል። ሆኖም ይሖዋ በተለያየ መንገድ ጠብቋቸዋል። ወላጅ ከሆንክ፣ ልጅህ እነዚህ የይሖዋ አገልጋዮች ያጋጠማቸውን መከራ በመቋቋም እምነታቸውን ጠብቀው መኖር የቻሉት እንዴት እንደሆነ እንዲገነዘብ እርዳው።

ይሖዋ አሥሩን መቅሰፍቶች በመጠቀም ከግብፅ አማልክት ይበልጥ ኃያል መሆኑን አሳይቷል። በጥንት ዘመን ይሖዋ ሕዝቦቹን የጠበቀው እንዴት እንደሆነና አሁንም ሕዝቦቹን የሚጠብቀው እንዴት እንደሆነ ጎላ አድርገህ ግለጽ።

በዚህ ክፍል ውስጥ

ትምህርት 14

አምላክን የታዘዘ ባሪያ

ዮሴፍ ትክክል የሆነውን ነገር አድርጓል፤ ሆኖም ከባድ መከራ ደርሶበታል። ይህ የሆነው ለምንድን ነው?

ትምህርት 15

ይሖዋ ዮሴፍን አልረሳውም

ዮሴፍ ከቤተሰቡ በጣም ርቆ ይገኝ የነበረ ቢሆንም አምላክ አልተለየውም።

ትምህርት 16

ኢዮብ ማን ነበር?

ችግሮች ቢደርሱበትም ይሖዋን ታዟል።

ትምህርት 17

ሙሴ ይሖዋን ለማምለክ መረጠ

ሙሴ ሕፃን በነበረበት ወቅት እናቱ በዘዴ ሕይወቱን አትርፋለች።

ትምህርት 18

በእሳት የተያያዘው ቁጥቋጦ

እሳቱ ቁጥቋጦውን ያላቃጠለው ለምንድን ነው?

ትምህርት 19

የመጀመሪያዎቹ ሦስት መቅሰፍቶች

ትዕቢተኛ የነበረው ፈርዖን አምላክ ያዘዘውን ቀላል ነገር ለመፈጸም ፈቃደኛ ባለመሆኑ በሕዝቡ ላይ መከራ እንዲመጣ አድርጓል።

ትምህርት 20

ስድስቱ መቅሰፍቶች

እነዚህ መቅሰፍቶች ከመጀመሪያዎቹ ሦስት መቅሰፍቶች የሚለዩት በምንድን ነው?

ትምህርት 21

አሥረኛው መቅሰፍት

ይህ መቅሰፍት በጣም አስከፊ ከመሆኑ የተነሳ ትዕቢተኛው ፈርዖን እንኳ ሕዝቡን ለመልቀቅ ፈቃደኛ ሆኗል።

ትምህርት 22

በቀይ ባሕር የተፈጸመው ተአምር

ፈርዖን ከአሥሩ መቅሰፍቶች መትረፍ የቻለ ቢሆንም ከዚህኛው የአምላክ ተአምር ማምለጥ ይችል ይሆን?