በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የክፍል 5 ማስተዋወቂያ

የክፍል 5 ማስተዋወቂያ

እስራኤላውያን ቀይ ባሕርን ከተሻገሩ ከሁለት ወራት በኋላ ወደ ሲና ተራራ ደረሱ። በዚያም ይሖዋ ልዩ ሕዝቡ እንዲሆኑ ከእስራኤላውያን ጋር ቃል ኪዳን ገባ። እስራኤላውያንን ጠብቋቸዋል፤ እንዲሁም የሚያስፈልጋቸውን ነገር በሙሉ አሟልቶላቸዋል፤ የሚበሉት መና፣ የማያረጅ ልብስ እንዲሁም ምንም ሳይፈሩ ተረጋግተው የሚኖሩበት ቦታ ሰጥቷቸዋል። ወላጅ ከሆንክ፣ ልጅህ ይሖዋ ለእስራኤላውያን ሕጉን፣ የማደሪያ ድንኳኑን እንዲሁም የክህነት ሥርዓቱን የሰጣቸው ለምን እንደሆነ እንዲገነዘብ እርዳው። ቃልን መጠበቅ፣ ትሑት መሆን እንዲሁም ምንጊዜም ለይሖዋ ታማኝ መሆን ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ ጎላ አድርገህ ግለጽ።

በዚህ ክፍል ውስጥ

ትምህርት 23

እስራኤላውያን ለይሖዋ ቃል ገቡ

እስራኤላውያን በሲና ተራራ አቅራቢያ በሰፈሩበት ወቅት ለይሖዋ ቃል ገብተው ነበር።

ትምህርት 24

ቃላቸውን አልጠበቁም

ሙሴ አሥርቱን ትእዛዛት እየተቀበለ በነበረበት ወቅት ሕዝቡ ከባድ ኃጢአት ፈጸመ።

ትምህርት 25

ለአምልኮ የሚያገለግል የማደሪያ ድንኳን

በዚህ ልዩ ድንኳን ውስጥ የቃል ኪዳኑ ታቦት ይቀመጥ ነበር።

ትምህርት 26

አሥራ ሁለቱ ሰላዮች

ኢያሱና ካሌብ የከነአንን ምድር ከሰለሉት ሌሎች አሥር ሰላዮች የተለዩ ነበሩ።

ትምህርት 27

በይሖዋ ላይ ዓመፁ

ቆሬ፣ ዳታን፣ አቤሮንና ሌሎች 250 ሰዎች ይሖዋን በተመለከተ ያላስተዋሉት አንድ ትልቅ እውነታ ነበር።

ትምህርት 28

የበለዓም አህያ ተናገረች

አህያዋ በለዓም ማየት ያልቻለውን መልአክ አየች።