በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የክፍል 10 ማስተዋወቂያ

የክፍል 10 ማስተዋወቂያ

ይሖዋ ሁሉንም የሚገዛ ንጉሥ ነው። ከጥንት ዘመን አንስቶ ሁሉንም ነገር ሲቆጣጠር ኖሯል፤ ወደፊትም ቢሆን ሁሉንም ነገር የሚቆጣጠረው እሱ ነው። ለምሳሌ ያህል፣ ኤርምያስ ጉድጓድ ውስጥ ተጥሎ በነበረበት ወቅት ከሞት ታድጎታል። ሲድራቅን፣ ሚሳቅንና አብደናጎን ደግሞ ከእቶን እሳት ውስጥ አውጥቷቸዋል፤ እንዲሁም ዳንኤልን ከአንበሶች አድኖታል። አስቴርም ሕዝቧን ማዳን እንድትችል ረድቷታል። ከዚህም ሌላ ይሖዋ ክፋት ለዘላለም እንዲቀጥል አይፈቅድም። ስለ ግዙፉ ምስልና ስለ ትልቁ ዛፍ የሚናገሩት ትንቢቶች የይሖዋ መንግሥት በቅርቡ ክፋትን በሙሉ አስወግዶ ምድርን እንደሚገዛ ያረጋግጣሉ።

በዚህ ክፍል ውስጥ

ትምህርት 57

ይሖዋ ኤርምያስን እንዲሰብክ ላከው

ወጣቱ ነቢይ የተናገረው ነገር የይሁዳን ሽማግሌዎች በጣም አበሳጫቸው።

ትምህርት 58

ኢየሩሳሌም ጠፋች

የይሁዳ ሕዝብ የሐሰት አማልክትን ማምለካቸውን ቀጠሉ፤ ስለዚህ ይሖዋ ተዋቸው።

ትምህርት 59

ይሖዋን የታዘዙ አራት ልጆች

አይሁዳውያን ወጣቶች በባቢሎን ንጉሥ በናቡከደነጾር ቤተ መንግሥት ውስጥ በነበሩበት ጊዜም ጭምር ለይሖዋ ታማኝ ለመሆን ወስነው ነበር።

ትምህርት 60

ለዘላለም ጸንቶ የሚኖር መንግሥት

ዳንኤል ናቡከደነጾር ያየው ሕልም ትርጉም ምን እንደሆነ ተናገረ።

ትምህርት 61

ለወርቁ ምስል አልሰገዱም

ሲድራቅ፣ ሚሳቅና አብደናጎ የባቢሎን ንጉሥ ላሠራው የወርቅ ምስል ለመስገድ ፈቃደኛ አልሆኑም።

ትምህርት 62

በትልቅ ዛፍ የተመሰለ መንግሥት

ናቡከደነጾር ያየው ሕልም ወደፊት የሚገጥመውን ሁኔታ የሚገልጽ ነበር።

ትምህርት 63

በግድግዳው ላይ የታየው ጽሑፍ

ይህ ጽሑፍ የታየው መቼ ነው? ትርጉሙስ ምንድን ነው?

ትምህርት 64

ዳንኤል አንበሶች ጉድጓድ ውስጥ ተጣለ

ልክ እንደ ዳንኤል በየቀኑ ወደ ይሖዋ ጸልይ!

ትምህርት 65

አስቴር ሕዝቧን ከጥፋት አዳነች

አስቴር ከሌላ አገር የመጣችና ወላጆቿ የሞቱባት ብትሆንም እንኳ ንግሥት ለመሆን በቅታለች።

ትምህርት 66

ዕዝራ የአምላክን ሕግ አስተማረ

እስራኤላውያን፣ ዕዝራ የሕጉን መጽሐፍ ካነበበላቸው በኋላ ለአምላክ ቃል ገቡ።

ትምህርት 67

የኢየሩሳሌም ግንብ

ነህምያ ጠላቶቹ ጥቃት ለመሰንዘር እንዳሰቡ ቢያውቅም ያልፈራው ለምንድን ነው?