መዝሙር 17
“እፈልጋለሁ”
(ሉቃስ 5:13)
-
1. ደግ፣ ሩኅሩኅ አሳቢ ነበር፣
ክርስቶስ ሲኖር በምድር።
ያስደስተው ነበር
ሰዎችን መርዳት፤
ለሌሎች ጊዜውን መስጠት።
አልረሳም ችግረኞችን፤
ፈውሷል የታመሙትን።
ተል’ኮውን ተወጣ በደስታ፤
“’ፈልጋለሁ” ብሏል ጌታ።
-
2. ክርስቶስ ነው ምሳሌያችን፤
ፈለጉን ’ንከተላለን።
እውነትን ስንሰብክ
’ንሁን አፍቃሪ፣
ደግና ሰውን አክባሪ።
ወንድሞች ሲቸግራቸው
በምንችለው እንርዳቸው።
አጋር፣ ወላጅ ያጡ ሲቸገሩ
‘መርዳት ’ፈልጋለሁ’ በሉ።