መዝሙር 19
የጌታ ራት
-
1. ይሖዋ የሰማዩ አባት፣
የዛሬዋ ቀን ቅዱስ ናት!
ከዘመናት በፊት ተገለጠ ክብርህ፤
ፍቅርህ፣ ፍትሕ፣ ጥበብ፣ ኃይልህ።
አዳንካቸው በፋሲካ ’ለት፤
ነፃ ወጡ ከባርነት፤
ከጊዜ በኋላም ጌታችን ሞተልን፤
የፋሲካው በግ ተሠዋልን።
-
2. ፊታችን ያሉት ቂጣና ወይን
ያስታውሱናል ፍቅርህን።
ልጅህ ታዛዥ ሆኖ
ሕይወቱን ሰጥቶናል፤
የሰው ልጆችን አድኗል።
ይህን ስጦታ አንረሳውም፤
አይወጣም ከልባችንም።
የክርስቶስ ቤዛ
ሞትን ድል ማድረጉን፣
እናስባለን ውለታውን።
-
3. በፊትህ ቀርበናል በዚህ ቀን፤
ያንተን ግብዣ ተቀብለን።
ላሳየኸን ፍቅር
በመስጠት ልጅህን፣
አንተን ከልብ ለማመስገን።
ይህ በዓል አንተን ያስከብራል፤
በእምነት ያበረታናል።
እንኑር ሁልጊዜ በክርስቶስ ትም’ርት፤
ለማግኘት የዘላለም ሕይወት።
(በተጨማሪም ሉቃስ 22:14-20ን እና 1 ቆሮ. 11:23-26ን ተመልከት።)