በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

መዝሙር 32

ከይሖዋ ጎን ቁም!

ከይሖዋ ጎን ቁም!

(ዘፀአት 32:26)

  1. 1. ግራ ገብቶን ነበር እጅግ አዝነን፣

    በሐሰት ትምህርቶች ተተብትበን፤

    ስለ አምላክ መንግሥት ስንሰማ ግን

    ፈነደቀ ልባችን።

    (አዝማች)

    ከይሖዋ ጎን ቁም፤ ተደሰት በሱም።

    ከቶ አይተውህም፤ ሂድ በሱ ብርሃን።

    የሰላም ምሥራች፣ አብስር ለሰዎች።

    ይስፋፋ መንግሥቱ፤ ይታይ እድገቱ።

  2. 2. ባንድነት ከይሖዋ ጎን ቆመን

    ለሰዎች ምሥራች እንሰብካለን።

    ሰዎች መርጠው ካምላክ ጎን ’ንዲቆሙ

    ግብዣው ይቅረብ ለሁሉ።

    (አዝማች)

    ከይሖዋ ጎን ቁም፤ ተደሰት በሱም።

    ከቶ አይተውህም፤ ሂድ በሱ ብርሃን።

    የሰላም ምሥራች፣ አብስር ለሰዎች።

    ይስፋፋ መንግሥቱ፤ ይታይ እድገቱ።

  3. 3. አንፈራም የሰይጣንን ጥቃት።

    በአምላክ ላይ አለን ሙሉ እምነት።

    አነስተኛ ቢሆንም ቁጥራችን፣

    ይሖዋ ነው ኃይላችን።

    (አዝማች)

    ከይሖዋ ጎን ቁም፤ ተደሰት በሱም።

    ከቶ አይተውህም፤ ሂድ በሱ ብርሃን።

    የሰላም ምሥራች፣ አብስር ለሰዎች።

    ይስፋፋ መንግሥቱ፤ ይታይ እድገቱ።

(በተጨማሪም መዝ. 94:14⁠ን፣ ምሳሌ 3:5, 6⁠ን እና ዕብ. 13:5⁠ን ተመልከት።)