መዝሙር 125
“መሐሪዎች ደስተኞች ናቸው”
(ማቴዎስ 5:7)
-
1. አምላካችን መሐሪ ነው፤
በደስታ ነው የሚምረው።
ለጋስ ነው፤ መስጠት ይወዳል፤
ሕዝቦቹን ይንከባከባል።
ይቅር ባይ አምላክ ነው እሱ፤
ኃጢያተኞች ሲመለሱ።
አፈር እንደሆንን ያውቃል፤
ደግ አምላክ ነው፤ ይምረናል።
-
2. በፈጸምነው ኃጢያት ምክንያት
ስንጠይቅ ያምላክን ምሕረት፣
ጌታችን እንዳስተማረን
በጸሎት ’ንማጸናለን፦
‘ሌሎችን ይቅር እንዳልን
አምላክ ሆይ፣ እኛንም ማረን።’
ከልባችን ይቅር ማለት
ይሰጠናል ሰላም፣ እረፍት።
-
3. ለሰዎች እናሳይ ምሕረት፤
ለጋሶች እንሁን የእውነት።
ምንም ብድራት ሳንጠብቅ
ለሰዎች መልካም እናድርግ።
አምላካችን ይህን አይቶ
ይባርከናል አሟልቶ።
መሐሪዎች ደስተኞች፣
ናቸው በአምላክ ፊት ውቦች።
(በተጨማሪም ማቴ. 6:2-4, 12-14ን ተመልከት።)