መዝሙር 141
ሕይወት ተአምር ነው
-
1. ልጅ መወለዱ፣ ዝናብ መጣሉ፣
የፀሐይ ደማቅ ጮራ፣ የ’ህል ዛላ፣
ሁሉም የአምላክ ስጦታ ናቸው፤
በሕይወት የኖርነው በሱ ተአምር ነው።
(አዝማች)
እንዴት ’ናመስግነው፣ ለዚህ ስጦታው?
እሱን መውደድ፣ ስጦታውን ማክበር ብቻ ነው።
በኛ ጥረት ቢሆን ጭራሽ አናገኘው፤
ሕይወት ስጦታ ነው፤ ሕይወት ተአምር ነው።
-
2. እንደ ኢዮብ ሚስት ተስፋ ’ሚቆርጡ፣
አምላክን ’ሚያማርሩ ሰዎች አሉ።
እኛ ግን ጌታን ’ናወድሳለን፤
በሕይወት እንድንኖር ስላደረገን።
(አዝማች)
እንዴት እናመስግን፣ ለዚህ ስጦታ?
ሰዎችን ’ንውደዳቸው እንስጣቸው ቦታ።
በኛ ጥረት ቢሆን ጭራሽ አናገኘው፤
ሕይወት ስጦታ ነው፤ ሕይወት ተአምር ነው።
(በተጨማሪም ኢዮብ 2:9ን፣ መዝ. 34:12ን፣ መክ. 8:15ን፣ ማቴ. 22:37-40ን እና ሮም 6:23ን ተመልከት።)