መዝሙር 147
የዘላለም ሕይወት ተስፋ ተሰጥቶናል
-
1. የዘላለም ሕይወት ተስፋ
ለሰው ልጆች ተሰጥቷል።
‘ገሮች ምድርን ይወርሳሉ’፤
ተስፋው ይፈጸማል።
(አዝማች)
የዘላለም ሕይወት
ተስፋ ተሰጥቶናል።
በ’ርግጥ ይፈጸማል፤
አምላክ ቃል ገብቷል።
-
2. ምድር ገነት ትሆናለች፤
ሰውም ፍጹም ይሆናል።
ይሖዋ በምድራችን ላይ
ሰላምን ያሰፍናል።
(አዝማች)
የዘላለም ሕይወት
ተስፋ ተሰጥቶናል።
በ’ርግጥ ይፈጸማል፤
አምላክ ቃል ገብቷል።
-
3. በቅርብ ሙታን ይነሳሉ፤
ያኔ ሐዘን ይረሳል።
ይሖዋ በርኅራኄው
እንባን ካይን ያብሳል።
(አዝማች)
የዘላለም ሕይወት
ተስፋ ተሰጥቶናል።
በ’ርግጥ ይፈጸማል፤
አምላክ ቃል ገብቷል።