በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ጥናት 3

ጥያቄዎችን መጠቀም

ጥያቄዎችን መጠቀም

ማቴዎስ 16:13-16

ፍሬ ሐሳብ፦ አድማጮችህ ለመልእክቱ ጉጉት እንዲያድርባቸውና ተመስጠው እንዲከታተሉህ ለማድረግ፣ ነጥቡን አሳማኝ በሆነ መንገድ ለማስረዳት እንዲሁም ዋና ዋና ነጥቦችን ለማጉላት ጥያቄዎችን በተገቢው መንገድ ተጠቀም።

ይህን ማድረግ የምትችለው እንዴት ነው?

  • አድማጮችህ ጉጉት እንዲያድርባቸውና ተመስጠው እንዲከታተሉህ አድርግ። አድማጮች ስለ ትምህርቱ ቆም ብለው እንዲያስቡ ወይም መልሱን ለማወቅ እንዲጓጉ የሚያደርጉ ጥያቄዎችን ተጠቀም

  • ነጥቡን አሳማኝ በሆነ መንገድ አስረዳ። አድማጮች ትክክለኛው መደምደሚያ ላይ እንዲደርሱ የሚረዱ ጥያቄዎችን በማንሳት ትምህርቱን አሳማኝና ግልጽ በሆነ መንገድ አቅርብ።

  • ዋና ዋና ነጥቦችን አጉላ። የማወቅ ፍላጎት የሚቀሰቅሱ ጥያቄዎችን በመጠየቅ ቁልፍ ነጥቦችን ማስተዋወቅ ትችላለህ። አንድ አስፈላጊ ነጥብ ካብራራህ በኋላ ወይም ደግሞ ንግግርህን ስትደመድም የክለሳ ጥያቄዎችን ተጠቀም።