በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የማዕረግ ስሞች

የማዕረግ ስሞች

ክርስቲያኖች በሃይማኖታዊ የማዕረግ ስሞች ሊጠሩ ይገባል?

ዮሐ 5:41

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ሉቃስ 18:18, 19—ኢየሱስ በባሕርይው ጥሩ ቢሆንም “ጥሩ መምህር” በሚለው የማዕረግ ስም መጠራት አልፈለገም፤ ለጥሩነቱ እውቅና ሊሰጠው የሚገባው ይሖዋ ብቻ እንደሆነ ተናግሯል

ክርስቲያኖች ሌሎች ሰዎችን እንደ “አባት” ወይም “መሪ” ባሉ ሃይማኖታዊ የማዕረግ ስሞች መጥራት የሌለባቸው ለምንድን ነው?

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ማቴ 23:9-12—ኢየሱስ ተከታዮቹ እንደ “አባት” ወይም “መሪ” ያሉ የማዕረግ ስሞችን እንዳይጠቀሙ ከልክሏል

    • 1ቆሮ 4:14-17—ሐዋርያው ጳውሎስ ለብዙዎች እንደ አባት ቢሆንም ‘አባ ጳውሎስ’ ተብሎ ወይም በሌላ መሰል መጠሪያ የተጠራበትን ቦታ አናገኝም

ክርስቲያኖች አንዳቸው ሌላውን እንደ ወንድም ወይም እህት ማየትና እንደዚያ ብለው መጥራት ያለባቸው ለምንድን ነው?

ማቴ 23:8

በተጨማሪም ሥራ 12:17፤ 18:18፤ ሮም 16:1⁠ን ተመልከት

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ማቴ 12:46-50—ኢየሱስ የእምነት አጋሮቹ፣ መንፈሳዊ ወንድሞቹና እህቶቹ እንደሆኑ ተናግሯል

ክርስቲያኖች የመንግሥት ባለሥልጣናትን፣ መሪዎችንና ዳኞችን በማዕረግ ስማቸው መጥራታቸው ተገቢ የሆነው ለምንድን ነው?

ሮም 13:1, 7፤ 1ጴጥ 2:17

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ሥራ 26:1, 2, 25—ሐዋርያው ጳውሎስ እንደ አግሪጳ እና ፊስጦስ ያሉ ገዢዎችን ሲጠራ የማዕረግ ስማቸውን ተጠቅሟል