ወላጆች
ይሖዋ ጋብቻን ካቋቋመባቸው ምክንያቶች አንዳንዶቹ ምንድን ናቸው?
ወላጆች ልጆቻቸውን እንዴት ሊያዩአቸው ይገባል?
በተጨማሪም “ልጆች፤ ወጣቶች” የሚለውን ተመልከት
-
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
-
ዘፍ 33:4, 5—ያዕቆብ ልጆቹን ከይሖዋ ያገኛቸው በረከቶች አድርጎ ተመልክቷቸዋል
-
ዘፀ 1:15, 16, 22፤ 2:1-4፤ 6:20—የሙሴ ወላጆች የሆኑት አምራምና ዮካቤድ እሱን ከአደጋ ለመጠበቅ ሲሉ ሕይወታቸውን አደጋ ላይ ጥለዋል
-
ወላጆች ከልጆቻቸው ጋር በተያያዘ ምን ኃላፊነት አለባቸው?
ልጆችን በይሖዋ መንገድ ማሠልጠን ምን ጥቅም አለው?
በተጨማሪም 2ጢሞ 3:14, 15ን ተመልከት
-
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
-
1ሳሙ 2:18-21, 26፤ 3:19—የሳሙኤል ወላጆች በማደሪያው ድንኳን እንዲያገለግል ልጃቸውን ሰጥተዋል፤ ይሁንና አዘውትረው እየሄዱ ይጠይቁት እንዲሁም የሚያስፈልገውን ነገር ይወስዱለት ነበር፤ ሳሙኤል ካደገ በኋላ መንፈሳዊ ሰው ሊሆን ችሏል
-
ሉቃስ 2:51, 52—ኢየሱስ፣ ፍጹም ባይሆኑም እንኳ ለወላጆቹ ሁልጊዜ ይገዛ ነበር
-
ወላጆች ልጆቻቸውን ለማሳደግ የሚረዳ መመሪያ ከየት ማግኘት ይችላሉ?
አንድ ልጅ አምላክን በሚወድ ቤተሰብ ውስጥ አድጎም እንኳ ይሖዋን ማገልገሉን ሊተው የሚችለው ለምንድን ነው?
ወላጆች የአምላክን መንገዶች ለልጆቻቸው ማስተማር መጀመር ያለባቸው መቼ ነው?
-
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
-
ዘዳ 29:10-12, 29፤ 31:12፤ ዕዝራ 10:1 —የይሖዋን መንገዶች ለመማር ከሚሰበሰበው ሕዝብ መካከል ልጆችም ይገኙበታል
-
ሉቃስ 2:41-52—ዮሴፍና ማርያም የፋሲካ በዓል በሚከበርበት ወቅት ኢየሱስን ጨምሮ ልጆቻቸውን በኢየሩሳሌም ወደሚገኘው ቤተ መቅደስ የመውሰድ ልማድ ነበራቸው
-
ወላጆች ልጆቻቸውን ሊጎዷቸው ከሚችሉ ሰዎች እንዲጠብቁ የትኞቹ የመጽሐፍ ቅዱስ ምሳሌዎች ትምህርት ይሆኗቸዋል?
-
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
-
ዘፀ 19:4፤ ዘዳ 32:11, 12—ይሖዋ ጫጩቶቿን ከምትሸከም፣ ከምትጠብቅና ከምትንከባከብ ንስር ጋር ራሱን አመሳስሏል
-
ኢሳ 49:15—ይሖዋ አገልጋዮቹን ለመንከባከብና ለመጠበቅ ቃል ገብቷል፤ ይህ የይሖዋ ርኅራኄ የምታጠባ እናት ለልጇ ካላት ስሜትም እንኳ የላቀ ነው
-
ማቴ 2:1-16—ሰይጣን፣ አረማውያን ኮከብ ቆጣሪዎችን ወደ ክፉው ንጉሥ ሄሮድስ በመምራት ሕፃኑን ኢየሱስን ሊያስገድለው ሞክሯል፤ ይሖዋ ግን ዮሴፍ ቤተሰቡን ይዞ ወደ ግብፅ እንዲሄድ በመንገር ልጁን ጠብቆታል
-
ማቴ 23:37—ኢየሱስ፣ ዶሮ ጫጩቶቿን በክንፎቿ ሥር በመሰብሰብ እንደምትጠብቃቸው ሁሉ እሱም ሕዝቡን መርዳት እንደሚፈልግ ተናግሯል
-
ወላጆች ልጆቻቸውን ስለ ፆታ ማስተማር ያለባቸው ለምንድን ነው?
-
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
-
ዘሌ 15:2, 3, 16, 18, 19፤ ዘዳ 31:10-13—የሙሴ ሕግ ስለ ፆታ ጉዳዮች በግልጽ ይናገራል፤ ይህ ሕግ ለሕዝቡ በሚነበብበት ወቅት ደግሞ ልጆችም እንዲገኙ ይሖዋ አዟል
-
መዝ 139:13-16—መዝሙራዊው ዳዊት የመራባት ሥርዓትን ጨምሮ የሰው አካል ስለተፈጠረበት አስደናቂ መንገድ ይሖዋን አወድሶታል
-
ምሳሌ 2:10-15—ከይሖዋ የሚገኘው እውቀትና ጥበብ ክፉና ተንኮለኛ ከሆኑ ሰዎች ይጠብቀናል
-
ተግሣጽ በፍቅር ሊሰጥ የሚገባው ለምንድን ነው?
ምሳሌ 13:24፤ 29:17፤ ኤር 30:11፤ ኤፌ 6:4
በተጨማሪም መዝ 25:8፤ 145:9፤ ቆላ 3:21ን ተመልከት
-
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
-
መዝ 32:1-5—ንጉሥ ዳዊት የይሖዋ ተግሣጽ ከብዶታል፤ ሆኖም ይሖዋ ከኃጢአታቸው ልባዊ ንስሐ የሚገቡ ሰዎችን ይቅር እንደሚል ማወቁ አጽናንቶታል
-
ዮናስ 4:1-11—ነቢዩ ዮናስ፣ ይሖዋን በቁጣና አክብሮት በጎደለው መንገድ አነጋግሮታል፤ ሆኖም ይሖዋ ምሕረት ስለማሳየት በትዕግሥት አስተምሮታል
-
ተግሣጽ የፍቅር መግለጫ ተደርጎ ሊታይ የሚገባው ለምንድን ነው?
በተጨማሪም ምሳሌ 15:32፤ ራእይ 3:19ን ተመልከት