በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ነጠላነት

ነጠላነት

ነጠላነት እንደ ስጦታ የሚታየው ከምን አንጻር ነው?

ነጠላ የሆነን ክርስቲያን እንዲያገባ መገፋፋት ስህተት የሆነው ለምንድን ነው?

1ቆሮ 7:28, 32-35፤ 1ተሰ 4:11

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ሮም 14:10-12—ሐዋርያው ጳውሎስ በእምነት አጋራችን ላይ መፍረድ ስህተት የሆነበትን ምክንያት አብራርቷል

    • 1ቆሮ 9:3-5—ሐዋርያው ጳውሎስ እንዳያገባ የሚከለክለው ነገር አልነበረም፤ ሆኖም ነጠላነቱ አገልግሎቱ ላይ እንዲያተኩር አስችሎታል

ያላገቡ ሰዎች ደስተኛ ለመሆን ማግባት እንዳለባቸው ሊሰማቸው ይገባል?

1ቆሮ 7:8

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • መሳ 11:30-40—የዮፍታሔ ሴት ልጅ ዕድሜዋን ሙሉ አላገባችም፤ ሆኖም ትርጉም ያለው ሕይወት መርታለች

    • ሥራ 20:35—ክርስቶስ ከተናገረው ነገር እንደምንረዳው ለሌሎች ይሰጥ ስለነበር ባያገባም ደስተኛ ነበር

    • 1ተሰ 1:2-9፤ 2:12—ነጠላ የሆነው ሐዋርያው ጳውሎስ ከአገልግሎቱ ያገኛቸውን አስደሳችና አርኪ ውጤቶች ገልጿል

እንደ ማንኛውም የአምላክ አገልጋይ ሁሉ ነጠላ ክርስቲያኖችም ሥነ ምግባራዊ ንጽሕናቸውን መጠበቅ ያለባቸው ለምንድን ነው?

1ቆሮ 6:18፤ ገላ 5:19-21፤ ኤፌ 5:3, 4

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ምሳሌ 7:7-23—አንድ ወጣት ሥነ ምግባር በጎደላት ሴት ማባበያ መሸነፉ ምን መዘዝ እንዳስከተለበት ንጉሥ ሰለሞን ገልጿል

    • መኃ 4:12፤ 8:8-10—ሱላማዊቷ ወጣት በንጹሕ ምግባሯ ተመስግናለች

ነጠላ የሆነ ሰው ማግባት ማሰቡ ጥበብ የሚሆነው መቼ ነው?

1ቆሮ 7:9, 36

በተጨማሪም 1ተሰ 4:4, 5⁠ን ተመልከት