በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

አምልኮ

አምልኮ

ሊመለክ የሚገባው ማን ብቻ ነው?

ዘፀ 34:14፤ ዘዳ 5:8-10፤ ኢሳ 42:8

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ማቴ 4:8-10—ሰይጣን፣ ኢየሱስ አንድ ጊዜ ካመለከው የዓለምን መንግሥታት ሁሉ እንደሚሰጠው ቃል ገባለት፤ ኢየሱስ ግን ግብዣውን አልተቀበለም፤ መመለክ ያለበት ይሖዋ ብቻ እንደሆነ ተናገረ

    • ራእይ 19:9, 10—አንድ ኃያል መልአክ፣ ሐዋርያው ዮሐንስ አምልኮ አከል ክብር እንዲሰጠው አልፈቀደለትም

ይሖዋ እንድናመልከው የሚፈልገው እንዴት ነው?

ዮሐ 4:24፤ ያዕ 1:26, 27

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ኢሳ 1:10-17—ይሖዋ፣ የእሱን መሥፈርቶች ለመከተል አሻፈረኝ ያሉ ግብዝ ሰዎች የሚያቀርቡለትን የአምልኮ ሥርዓቶች አይቀበልም እንዲሁም ይጸየፋቸዋል

    • ማቴ 15:1-11—ይሖዋ በወግ ላይ የተመሠረተ አምልኮን እንደማይቀበል ኢየሱስ ተናግሯል፤ ምክንያቱም እንዲህ ያለው አምልኮ ሰዎች ያወጧቸውን ደንቦች ከአምላክ ሕጎች ያስቀድማል

የሚቻል በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ ይሖዋን ማምለክ ያለብን ከማን ጋር ነው?

ዕብ 10:24, 25

በተጨማሪም መዝ 133:1-3⁠ን ተመልከት

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ሥራ 2:40-42—በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበሩ ክርስቲያኖች ለጸሎት፣ አብረው ጊዜ ለማሳለፍና በመንፈስ መሪነት የተጻፉ ትምህርቶችን አብረው ለማጥናት ይሰበሰቡ ነበር

    • 1ቆሮ 14:26-40—ሐዋርያው ጳውሎስ የጉባኤ ስብሰባዎች ሥርዓታማና የሚያንጹ እንዲሆኑ መመሪያ ሰጥቷል፤ ዓላማውም ስብሰባው ላይ የተገኙት ሁሉ እንዲማሩና የሚተላለፈውን ትምህርት እንዲረዱ ነው

አምልኳችን በይሖዋ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኝ ምን ማድረግ አለብን?

ማቴ 7:21-24፤ 1ዮሐ 2:17፤ 5:3

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዕብ 11:6—ሐዋርያው ጳውሎስ ይሖዋን ተቀባይነት ባለው መንገድ ለማምለክ እምነት የግድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጿል

    • ያዕ 2:14-17, 24-26—የኢየሱስ ወንድም የሆነው ያዕቆብ፣ እምነታችን በሥራ የተደገፈ መሆን እንዳለበት ተናግሯል፤ ለተግባር የሚያነሳሳን እምነታችን ነው