በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ለውይይት የሚሆኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ርዕሶች

ለውይይት የሚሆኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ርዕሶች

ለውይይት የሚሆኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ርዕሶች

1. ሃይማኖት

  ሀ. እውነተኛው ሃይማኖት አንድ ብቻ ነው

አንድ ተስፋ፣ አንድ እምነት፣ አንድ ጥምቀት። ኤፌ 4:5, 13

ደቀ መዛሙርት የማድረግ ተልእኮ ተሰጥቶታል። ማቴ 28:19፤ ሥራ 8:12፤ 14:21

በፍሬው ይታወቃል። ማቴ 7:19, 20፤ ሉቃስ 6:43, 44፤ ዮሐ 15:8

በአባሎቹ መካከል ፍቅርና ስምምነት ይኖራል። ዮሐ 13:35፤ 1ቆሮ 1:10፤ 1ዮሐ 4:20

 ለ. የሐሰት ትምህርት መወገዙ የተገባ ነው

ኢየሱስ የሐሰት ትምህርትን አውግዟል። ማቴ 23:15, 23, 24፤ 15:4-9

እንደዚያ ያደረገው ለታወሩት ጥበቃ ሲል ነው። ማቴ 15:14

እውነት ነፃ አውጥቶ የኢየሱስ ደቀ መዛሙርት አድርጓቸዋል። ዮሐ 8:31, 32

 ሐ. ሃይማኖታችን ስህተት መሆኑ ከተረጋገጠ የግድ መለወጥ ያስፈልገናል

እውነት ነፃ ያወጣል፤ ብዙዎች እንደተሳሳቱ ያሳያል። ዮሐ 8:31, 32

እስራኤላውያንና ሌሎች ፊተኛውን አምልኳቸውን ትተዋል። ኢያሱ 24:15፤ 2ነገ 5:17

የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች የቀድሞ አስተሳሰባቸውን ለውጠዋል። ገላ 1:13, 14፤ ሥራ 3:17, 19

ጳውሎስ ሃይማኖቱን ለውጧል። ሥራ 26:4-6

መላው ዓለም ተታሏል፤ አስተሳሰባችንን መለወጥ ያስፈልገናል። ራእይ 12:9፤ ሮም 12:2

 መ. “ሁሉም ሃይማኖቶች ጥሩ ነገር” ያላቸው ቢመስሉም አምላክ እንደሚቀበላቸው ማረጋገጫ አይሆንም

አምልኮን በተመለከተ መሥፈርት የሚያወጣው አምላክ ነው። ዮሐ 4:23, 24፤ ያዕ 1:27

ከአምላክ ፈቃድ ጋር የማይስማማ ከሆነ ተቀባይነት የለውም። ሮም 10:2, 3

ሰዎች “መልካም ሥራዎች” የሚሏቸውን ነገሮች አምላክ ላይቀበላቸው ይችላል። ማቴ 7:21-23

የሚታወቀው በፍሬው ነው። ማቴ 7:20

2. ሃይማኖትን መቀላቀል

  ሀ. ከሌሎች ሃይማኖቶች ጋር ኅብረት መፍጠር በአምላክ ዘንድ ተቀባይነት የለውም

መንገዱ ጠባብና አንድ ብቻ ነው፤ የሚያገኙት ጥቂቶች ናቸው። ኤፌ 4:4-6፤ ማቴ 7:13, 14

የሐሰት ትምህርት እንደሚበክል ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል። ማቴ 16:6, 12፤ ገላ 5:9

ከሐሰት ሃይማኖት እንድንለይ ታዘናል። 2ጢሞ 3:5፤ 2ቆሮ 6:14-17፤ ራእይ 18:4

 ለ. “ሁሉም ሃይማኖቶች ጥሩ ነገር አላቸው” የሚባለው እውነት አይደለም

አንዳንዶች ቅንዓት አላቸው፤ ሆኖም ከአምላክ ፈቃድ ጋር የሚስማማ አይደለም። ሮም 10:2, 3

መጥፎ ነገር ሌላውን መልካም ነገር ሁሉ ያበላሻል። 1ቆሮ 5:6፤ ማቴ 7:15-17

የሐሰት አስተማሪዎች ጥፋት ያመጣሉ። 2ጴጥ 2:1፤ ማቴ 12:30፤ 15:14

ንጹሕ አምልኮ ለይሖዋ ብቻ የተወሰነ አምልኮ ማቅረብን ይጠይቃል። ዘዳ 6:5, 14, 15

3. ለማርያም የሚቀርብ አምልኮ

  ሀ. ማርያም የኢየሱስ እናት እንጂ “የአምላክ እናት” አልነበረችም

አምላክ መጀመሪያ የለውም። መዝ 90:2፤ 1ጢሞ 1:17

የአምላክ ልጅ በምድር ሳለ ማርያም እናቱ ነበረች። ሉቃስ 1:35

 ለ. ማርያም “ለሁልጊዜው ድንግል” ሆና አልኖረችም

ዮሴፍን አግብታለች። ማቴ 1:19, 20, 24, 25

ከኢየሱስ በተጨማሪ ሌሎች ልጆች ወልዳለች። ማቴ 13:55, 56፤ ሉቃስ 8:19-21

እነሱ በወቅቱ “መንፈሳዊ ወንድሞቹ” አልነበሩም። ዮሐ 7:3, 5

4. ሐሰተኛ ነቢያት

  ሀ. ሐሰተኛ ነቢያት እንደሚመጡ አስቀድሞ ተነግሯል፤ በሐዋርያት ዘመን ነበሩ

ሐሰተኛ ነቢያትን መለየት የሚቻልበት መንገድ። ዘዳ 18:20-22፤ ሉቃስ 6:26

እንደሚመጡ አስቀድሞ ተነግሯል፤ በፍሬያቸው ይታወቃሉ። ማቴ 24:23-26፤ 7:15-23

5. ሕይወት

  ሀ. ታዛዥ የሆኑ የሰው ልጆች የዘላለም ሕይወት እንደሚያገኙ ማረጋገጫ ተሰጥቷቸዋል

ሊዋሽ የማይችለው አምላክ የዘላለም ሕይወት ተስፋ ሰጥቷል። ቲቶ 1:2፤ ዮሐ 10:27, 28

እምነታቸውን በተግባር የሚያሳዩ ሁሉ የዘላለም ሕይወት እንደሚያገኙ ቃል ተገብቶላቸዋል። ዮሐ 11:25, 26

ሞት ይጠፋል። 1ቆሮ 15:26፤ ራእይ 21:4፤ 20:14፤ ኢሳ 25:8

 ለ. በሰማይ ሕይወት የሚያገኙት የክርስቶስ አካል የሆኑት ብቻ ናቸው

አምላክ እሱ በፈለገው መንገድ አባሎቹን ይመርጣል። ማቴ 20:23፤ 1ቆሮ 12:18

ከምድር የሚወሰዱት 144,000 ብቻ ናቸው። ራእይ 14:1, 4፤ 7:2-4፤ 5:9, 10

አጥማቂው ዮሐንስ እንኳ የሰማያዊው መንግሥት አባል አይሆንም። ማቴ 11:11

 ሐ. ቁጥራቸው ያልተወሰነ “ሌሎች በጎች” ምድራዊ ሕይወት እንደሚያገኙ ቃል ተገብቶላቸዋል

በሰማይ ከኢየሱስ ጋር የሚሆኑት ቁጥራቸው የተወሰነ ነው። ራእይ 14:1, 4፤ 7:2-4

“ሌሎች በጎች” የክርስቶስ ወንድሞች አይደሉም። ዮሐ 10:16፤ ማቴ 25:32, 40

አሁን ብዙ ሰዎች ከጥፋት ተርፈው ምድር ላይ ለመኖር እየተሰበሰቡ ነው። ራእይ 7:9, 15-17

ሌሎች ደግሞ በምድር ላይ ለመኖር ትንሣኤ ያገኛሉ። ራእይ 20:12፤ 21:4

6. መመሥከር

  ሀ. ሁሉም ክርስቲያኖች መመሥከር፣ ምሥራቹን መናገር አለባቸው

ተቀባይነት ለማግኘት ስለ ኢየሱስ በሰው ፊት መመሥከር አለብን። ማቴ 10:32

ቃሉን በተግባር በማዋል እምነታችንን በሥራ ማሳየት አለብን። ያዕ 1:22-24፤ 2:24

አዲሶችም አስተማሪዎች መሆን አለባቸው። ማቴ 28:19, 20

ለሕዝብ መመሥከር መዳን ያስገኛል። ሮም 10:10

 ለ. ደጋግሞ ወደ ሰዎች መሄድ፣ በምሥክርነቱ ሥራ መቀጠል ያስፈልጋል

ፍጻሜው እንደሚመጣ ማስጠንቀቂያ መሰጠት ይኖርበታል። ማቴ 24:14

ኤርምያስ ኢየሩሳሌም እንደምትጠፋ ለብዙ ዓመታት አስታውቋል። ኤር 25:3

እንደ ጥንቶቹ ክርስቲያኖች ሁሉ እኛም መመሥከራችንን ልናቆም አንችልም። ሥራ 4:18-20፤ 5:28, 29

 ሐ. ከደም ዕዳ ነፃ ለመሆን መመሥከር አለብን

እየቀረበ ስለመጣው ፍጻሜ ማስጠንቀቂያ መስጠት አለብን። ሕዝ 33:7፤ ማቴ 24:14

ይህን አለማድረግ በደም ዕዳ ተጠያቂ ያደርጋል። ሕዝ 33:8, 9፤ 3:18, 19

ጳውሎስ ከደም ዕዳ ነፃ ሆኗል፤ እውነትን በተሟላ ሁኔታ ሰብኳል። ሥራ 20:26, 27፤ 1ቆሮ 9:16

የምሥክርነቱ ሥራ የሚመሠክረውንም ሆነ የሚሰማውን ያድናል። 1ጢሞ 4:16፤ 1ቆሮ 9:22

7. መስቀል

  ሀ. ኢየሱስ እንዲዋረድ ሲባል ወንጀለኞች በሚሰቀሉበት እንጨት ላይ እንዲሰቀል ተደርጓል

ኢየሱስ ወንጀለኞች በሚሰቀሉበት እንጨት ወይም ግንድ ላይ ተሰቅሏል። ሥራ 5:30፤ 10:39፤ ገላ 3:13

ክርስቲያኖች የመከራውን እንጨት መሸከማቸው የሚደርስባቸውን ነቀፋ ለመቀበል ፈቃደኛ መሆናቸውን ያሳያል። ማቴ 10:38፤ ሉቃስ 9:23

 ለ. መመለክ የለበትም

ኢየሱስ የተሰቀለበትን እንጨት እንደ ጌጥ መጠቀም እሱን እንደማዋረድ ይቆጠራል። ዕብ 6:6፤ ማቴ 27:41, 42

መስቀልን ለአምልኮ መጠቀም ጣዖት አምልኮ ነው። ዘፀ 20:4, 5፤ ኤር 10:3-5

አሁን ኢየሱስ መንፈስ ነው፤ ገና እንደተሰቀለ አይደለም። 1ጢሞ 3:16፤ 1ጴጥ 3:18

8. መታሰቢያ በዓል፣ ቁርባን

  ሀ. የጌታ ራት መታሰቢያ በዓል

በፋሲካ ዕለት በዓመት አንድ ጊዜ ይከበራል። ሉቃስ 22:1, 17-20፤ ዘፀ 12:14

የክርስቶስ መሥዋዕታዊ ሞት መታሰቢያ ነው። 1ቆሮ 11:26፤ ማቴ 26:28

ሰማያዊ ተስፋ ያላቸው ይካፈላሉ። ሉቃስ 22:29, 30፤ 12:32, 37

አንድ ሰው ይህ ተስፋ እንዳለው የሚያውቀው እንዴት ነው? ሮም 8:15-17

 ለ. ቁርባን ቅዱስ ጽሑፋዊ ድጋፍ የለውም

የኃጢአት ይቅርታ ለማግኘት ደም መፍሰስ አለበት። ዕብ 9:22

ክርስቶስ ብቸኛው የአዲሱ ቃል ኪዳን መካከለኛ ነው። 1ጢሞ 2:5, 6፤ ዮሐ 14:6

ክርስቶስ ያለው በሰማይ ነው፤ ቄስ ወደ ምድር እንዲወርድ ሊያደርገው አይችልም። ሥራ 3:20, 21

የክርስቶስ መሥዋዕት በድጋሚ መቅረብ አያስፈልገውም። ዕብ 9:24-26፤ 10:11-14

9. መንግሥት

  ሀ. የአምላክ መንግሥት ለሰው ልጆች ምን ያመጣል?

የአምላክን ፈቃድ ያስፈጽማል። ማቴ 6:9, 10፤ መዝ 45:6፤ ራእይ 4:11

ንጉሥና ሕግ ያለው መስተዳድር ነው። ኢሳ 9:6, 7፤ 2:3፤ መዝ 72:1, 8

ክፋትን አስወግዶ ጠቅላላውን ምድር ይገዛል። ዳን 2:44፤ መዝ 72:8

በ1,000 ዓመት የግዛት ዘመን የሰው ልጆችን መጀመሪያ ላይ ወደነበረው ሁኔታ ይመልሳል፤ ገነትን ያመጣል። ራእይ 21:2-4፤ 20:6

 ለ. መግዛት የሚጀምረው የክርስቶስ ጠላቶች ገና እያሉ ነው

ክርስቶስ ከተነሳ በኋላ ረጅም ዘመን መጠበቅ ነበረበት። መዝ 110:1፤ ዕብ 10:12, 13

ሥልጣንን እንደሚይዝና ሰይጣንን እንደሚዋጋ ተገልጿል። መዝ 110:2፤ ራእይ 12:7-9፤ ሉቃስ 10:18

መንግሥቱ ከተቋቋመ በኋላ በምድር ላይ ወዮታ ይከሰታል። ራእይ 12:10, 12

በአሁኑ ጊዜ ያለው መከራ መንግሥቱን ደግፎ ለመቆም ጊዜው አሁን መሆኑን ያሳያል። ራእይ 11:15-18

 ሐ. በሰው ‘ልብ ውስጥ’ ያለም ሆነ በሰዎች ጥረት የሚመጣ አይደለም

መንግሥቱ በሰማይ እንጂ በምድር አይደለም። 2ጢሞ 4:18፤ 1ቆሮ 15:50፤ መዝ 11:4

በሰው ‘ልብ ውስጥ’ ያለ አይደለም፤ ኢየሱስ እየተናገረ የነበረው ለፈሪሳውያን ነው። ሉቃስ 17:20, 21

የዚህ ዓለም ክፍል አይደለም። ዮሐ 18:36፤ ሉቃስ 4:5-8፤ ዳን 2:44

መንግሥታትና የዓለም መሥፈርቶች በሌላ ይተካሉ። ዳን 2:44

10. መንፈስ፣ መናፍስታዊ ድርጊቶች

  ሀ. መንፈስ ቅዱስ ምንድን ነው?

ከአምላክ የሚወጣ ኃይል እንጂ ራሱን የቻለ አካል አይደለም። ሥራ 2:2, 3, 33፤ ዮሐ 14:17

አምላክ ለመፍጠር፣ ሰዎች መጽሐፍ ቅዱስን እንዲጽፉ ለማነሳሳት ወዘተ ተጠቅሞበታል። ዘፍ 1:2፤ ሕዝ 11:5

የክርስቶስ አካል አባላት በመንፈስ የተወለዱና የተቀቡ ናቸው። ዮሐ 3:5-8፤ 2ቆሮ 1:21, 22

በዛሬው ጊዜ የአምላክን ሕዝቦች ያበረታቸዋል እንዲሁም ይመራቸዋል። ገላ 5:16, 18

 ለ. ሕይወትን የሚያንቀሳቅሰው ኃይል መንፈስ ተብሏል

የሕይወት ኃይል ቀጣይ የሚሆነው በመተንፈስ ነው። ያዕ 2:26፤ ኢዮብ 27:3

ሕይወትን የሚያንቀሳቅሰው ኃይል በአምላክ እጅ ነው። ዘካ 12:1፤ መክ 8:8

የሰዎችና የእንስሳት የሕይወት ኃይል ባለቤት አምላክ ነው። መክ 3:19-21

ሰው ትንሣኤን ተስፋ በማድረግ መንፈሱን ለአምላክ ይሰጣል። ሉቃስ 23:46

 ሐ. መናፍስታዊ ድርጊቶች የአጋንንት ሥራ ስለሆኑ ልንርቃቸው ይገባል

የአምላክ ቃል ከመናፍስታዊ ድርጊቶች እንድንርቅ ያዛል። ኢሳ 8:19, 20፤ ዘሌ 19:31፤ 20:6, 27

ጥንቆላ የአጋንንት ሥራ ነው፤ ተወግዟል። ሥራ 16:16-18

ለጥፋት ይዳርጋል። ገላ 5:19-21፤ ራእይ 21:8፤ 22:15

ኮከብ ቆጠራ የተወገዘ ነው። ዘዳ 18:10-12፤ ኤር 10:2

11. መዳን

  ሀ. መዳን የሚገኘው ከአምላክ ሲሆን ይህም የሚሆነው በኢየሱስ ቤዛዊ መሥዋዕት አማካኝነት ነው

ሕይወት አምላክ በልጁ በኩል የሚሰጠን ስጦታ ነው። 1ዮሐ 4:9, 14፤ ሮም 6:23

መዳን የሚቻለው በኢየሱስ መሥዋዕት በኩል ብቻ ነው። ሥራ 4:12

“በሞት ጣር ላይ እያሉ ንስሐ በመግባት” ለመዳን የሚያበቃ ሥራ መሥራት አይቻልም። ያዕ 2:14, 26

ለመዳን ብርቱ ጥረት ማድረግ ያስፈልጋል። ሉቃስ 13:23, 24፤ 1ጢሞ 4:10

 ለ. “አንዴ የዳነ ለሁልጊዜው ድኗል” የሚለው አባባል ቅዱስ ጽሑፋዊ መሠረት የለውም

የመንፈስ ቅዱስ ተካፋይ የሆኑት ሊወድቁ ይችላሉ። ዕብ 6:4, 6፤ 1ቆሮ 9:27

ብዙ እስራኤላውያን ከግብፅ ቢድኑም በኋላ ጠፍተዋል። ይሁዳ 5

መዳን ወዲያው የሚገኝ ነገር አይደለም። ፊልጵ 2:12፤ 3:12-14፤ ማቴ 10:22

ወደኋላ የሚመለሱት ከበፊቱ የከፋ ሁኔታ ውስጥ ይገባሉ። 2ጴጥ 2:20, 21

 ሐ. “ሁሉም ሰው ይድናል” የሚለው አባባል ቅዱስ ጽሑፋዊ መሠረት የለውም

ለአንዳንዶች ንስሐ መግባት የማይቻል ነገር ነው። ዕብ 6:4-6

አምላክ በክፉዎች ሞት አይደሰትም። ሕዝ 33:11፤ 18:32

ይሁን እንጂ ፍቅር ዓመፅን ቸል ብሎ አያልፍም። ዕብ 1:9

ክፉዎች ይጠፋሉ። ዕብ 10:26-29፤ ራእይ 20:7-15

12. መጽሐፍ ቅዱስ

  ሀ. የአምላክ ቃል በመንፈስ መሪነት የተጻፈ ነው

ሰዎች እንዲጽፉ ያነሳሳቸው የአምላክ መንፈስ ነው። 2ጴጥ 1:20, 21

ትንቢቶችን ይዟል:- ዳን 8:5, 6, 20-22፤ ሉቃስ 21:5, 6, 20-22፤ ኢሳ 45:1-4

ጠቅላላው መጽሐፍ ቅዱስ በመንፈስ መሪነት የተጻፈና ጠቃሚ ነው። 2ጢሞ 3:16, 17፤ ሮም 15:4

 ለ. ለዘመናችን ጠቃሚ የሆነ መመሪያ ነው

የመጽሐፍ ቅዱስን መሠረታዊ ሥርዓቶች ችላ ማለት ለሞት ይዳርጋል። ሮም 1:28-32

የሰው ጥበብ ሊተካው አይችልም። 1ቆሮ 1:21, 25፤ 1ጢሞ 6:20

ብርቱ የሆነን ጠላት ለመመከት ያስችላል። ኤፌ 6:11, 12, 17

ሰውን በትክክለኛው አቅጣጫ ይመራል። መዝ 119:105፤ 2ጴጥ 1:19፤ ምሳሌ 3:5, 6

 ሐ. ለሁሉም ሕዝቦችና ዘሮች የተጻፈ ነው

መጽሐፍ ቅዱስን መጻፍ የተጀመረው በመካከለኛው ምሥራቅ አካባቢ ነው። ዘፀ 17:14፤ 24:12, 16፤ 34:27

አምላክ ያስጻፈው ለአውሮፓውያን ብቻ አይደለም። ሮም 10:11-13፤ ገላ 3:28

አምላክ ሁሉንም ዓይነት ሰዎች ይቀበላል። ሥራ 10:34, 35፤ ሮም 5:18፤ ራእይ 7:9, 10

13. ምስሎች

  ሀ. ምስሎችንና ቅርጻ ቅርጾችን ለአምልኮ መጠቀም አምላክን እንደማዋረድ ይቆጠራል

የአምላክን ምስል መሥራት የማይቻል ነገር ነው። 1ዮሐ 4:12፤ ኢሳ 40:18፤ 46:5፤ ሥራ 17:29

ክርስቲያኖች ከምስሎች እንዲርቁ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷቸዋል። 1ቆሮ 10:14፤ 1ዮሐ 5:21

አምላክ በመንፈስና በእውነት መመለክ አለበት። ዮሐ 4:24

 ለ. የምስል አምልኮ የእስራኤልን ሕዝብ ለጥፋት ዳርጎታል

አይሁዶች ምስሎችን እንዳያመልኩ ተከልክለው ነበር። ዘፀ 20:4, 5

ሊሰሙና ሊናገሩ አይችሉም፤ የሚሠሯቸው እንደነሱ ይሆናሉ። መዝ 115:4-8

ወጥመድና ጥፋት አምጥተዋል። መዝ 106:36, 40-42፤ ኤር 22:8, 9

 ሐ. በተወሰነ መጠንም ቢሆን አምልኮን ለሌላ መስጠት አልተፈቀደም

አምላክ በተወሰነ መጠንም ቢሆን አምልኮ ለሌሎች እንዲቀርብ አይፈልግም። ኢሳ 42:8

‘ጸሎትን የሚሰማው’ አምላክ ብቻ ነው። መዝ 65:1, 2

14. ምድር

  ሀ. አምላክ ለምድር ያለው ዓላማ

በምድር ላይ ፍጹማን ሰዎች የሚኖሩበት ገነት ተዘጋጅቶ ነበር። ዘፍ 1:28፤ 2:8-15

የአምላክ ዓላማ በእርግጥ ይፈጸማል። ኢሳ 55:11፤ 46:10, 11

ምድር ሰላማውያንና ፍጹማን በሆኑ ሰዎች ትሞላለች። መዝ 72:7፤ ኢሳ 45:18፤ 9:6, 7

በአምላክ መንግሥት አማካኝነት ገነት ተመልሶ ይቋቋማል። ማቴ 6:9, 10፤ ራእይ 21:3-5

 ለ. ፈጽሞ አትጠፋም ወይም ሰው አልባ አትሆንም

ግዑዟ ምድር ለሁልጊዜ ጸንታ ትኖራለች። መክ 1:4፤ መዝ 104:5

በኖኅ ጊዜ የጠፉት የሰው ልጆች እንጂ ምድር አልነበረችም። 2ጴጥ 3:5-7፤ ዘፍ 7:23

በዚያን ጊዜ የተፈጸመው ነገር በዘመናችንም ከጥፋት መትረፍ እንደሚቻል ይጠቁማል። ማቴ 24:37-39

ክፉዎች ይጠፋሉ፤ “እጅግ ብዙ ሕዝብ” ይተርፋል። 2ተሰ 1:6-9፤ ራእይ 7:9, 14

15. ሞት

  ሀ. የሞት መንስኤ

የሰው ልጅ ሕይወት ጅምር ፍጹም ነበር፤ ፍጻሜ የሌለው ሕይወት ከፊቱ ተዘርግቶለት ነበር። ዘፍ 1:28, 31

አለመታዘዝ የሞት ፍርድ አመጣ። ዘፍ 2:16, 17፤ 3:17, 19

ኃጢአትና ሞት ወደ አዳም ልጆች ሁሉ ተላልፈዋል። ሮም 5:12

 ለ. የሙታን ሁኔታ

አዳም ራሱ ነፍስ ነበር እንጂ ነፍስ አልተሰጠውም። ዘፍ 2:7፤ 1ቆሮ 15:45

የሚሞተው ነፍስ የሆነው ሰውየው ራሱ ነው። ሕዝ 18:4፤ ኢሳ 53:12፤ ኢዮብ 11:20

ሙታን አይሰሙም፤ ምንም አያውቁም። መክ 9:5, 10፤ መዝ 146:3, 4

ሙታን አንቀላፍተዋል፤ ትንሣኤ ይጠብቃሉ። ዮሐ 11:11-14, 23-26፤ ሥራ 7:60

 ሐ. ከሙታን ጋር መነጋገር ፈጽሞ አይቻልም

ሙታን መናፍስት ሆነው ከአምላክ ጋር እየኖሩ አይደለም። መዝ 115:17፤ ኢሳ 38:18

ከሙታን ጋር ለመነጋገር እንዳንሞክር ማስጠንቀቂያ ተሰጥቶናል። ኢሳ 8:19፤ ዘሌ 19:31

መናፍስት ጠሪዎችና ጠንቋዮች የተወገዙ ናቸው። ዘዳ 18:10-12፤ ገላ 5:19-21

16. ሥላሴ

  ሀ. አባት የሆነው አምላክ አንድ ነው፤ በጽንፈ ዓለም ውስጥ ከሁሉ የሚበልጠው እሱ ነው

አምላክ የሦስት አካላት ጥምረት አይደለም። ዘዳ 6:4፤ ሚል 2:10፤ ማር 10:18፤ ሮም 3:29, 30

ወልድ ፍጡር ነው፤ ከዚያ በፊት አምላክ ብቻውን ነበር። ራእይ 3:14፤ ቆላ 1:15፤ ኢሳ 44:6

አምላክ ምንጊዜም የጽንፈ ዓለም ገዥ ነው። ፊልጵ 2:5, 6፤ ዳን 4:35

አምላክ ከሁሉም በላይ ከፍ መደረግ ይኖርበታል። ፊልጵ 2:10, 11

 ለ. ወልድ ወደ ምድር ከመምጣቱ በፊትም ሆነ ከዚያ በኋላ ከአባቱ ያንሳል

ወልድ በሰማይ ሳለ ታዛዥ ነበር፤ ወደ ምድር የመጣው አባቱ ልኮት ነው። ዮሐ 8:42፤ 12:49

ምድር ላይ ሳለ ታዛዥ ነበር፤ አባቱ ይበልጠዋል። ዮሐ 14:28፤ 5:19፤ ዕብ 5:8

በሰማይ ከፍ ከፍ ተደርጓል፤ ያም ሆኖ ለአባቱ ይገዛል። ፊልጵ 2:9፤ 1ቆሮ 15:28፤ ማቴ 20:23

ይሖዋ የክርስቶስ ራስና አምላክ ነው። 1ቆሮ 11:3፤ ዮሐ 20:17፤ ራእይ 1:6

 ሐ. የአምላክና የክርስቶስ አንድነት

ምንጊዜም ፍጹም ስምምነት አላቸው። ዮሐ 8:28, 29፤ 14:10

አንድነታቸው በባልና በሚስት መካከል እንዳለው አንድነት ነው። ዮሐ 10:30፤ ማቴ 19:4-6

አማኞች በሙሉ ይኸው አንድነት ሊኖራቸው ይገባል። ዮሐ 17:20-22፤ 1ቆሮ 1:10

በክርስቶስ በኩል ይሖዋ ብቻ ለዘላለም ይመለካል። ዮሐ 4:23, 24

 መ. የአምላክ ቅዱስ መንፈስ የእሱ ኃይል ነው

ኃይል እንጂ ራሱን የቻለ አካል አይደለም። ማቴ 3:16፤ ዮሐ 20:22፤ ሥራ 2:4, 17, 33

በሰማይ ከአምላክና ከክርስቶስ ጋር የሚኖር ራሱን የቻለ አካል አይደለም። ሥራ 7:55, 56፤ ራእይ 7:10

አምላክ ዓላማዎቹን ለመፈጸም በፈለገው መንገድ ይጠቀምበታል። መዝ 104:30፤ 1ቆሮ 12:4-11

አምላክን የሚያገለግሉ መንፈሱን ይቀበላሉ፤ እንዲሁም በመንፈሱ ይመራሉ። 1ቆሮ 2:12, 13፤ ገላ 5:16

17. ሰማይ

  ሀ. ወደ ሰማይ የሚሄዱት 144,000 ብቻ ናቸው

ቁጥራቸው የተወሰነ ነው፤ ከክርስቶስ ጋር ነገሥታት ይሆናሉ። ራእይ 5:9, 10፤ 20:4

የመጀመሪያው ኢየሱስ ነው፤ ከዚያ በኋላ ሌሎች ተመርጠዋል። ቆላ 1:18፤ 1ጴጥ 2:21

ሌሎች ብዙ ሰዎች ምድር ላይ ይኖራሉ። መዝ 72:8፤ ራእይ 21:3, 4

144,000ዎቹ ሌሎች ያላገኙትን ልዩ ቦታ ያገኛሉ። ራእይ 14:1, 3፤ 7:4, 9

18. ሰንበት

  ሀ. ክርስቲያኖች የሰንበትን ቀን እንዲያከብሩ አይገደዱም

የኢየሱስ ሞት ሕጉን አስወግዶታል። ኤፌ 2:15

ክርስቲያኖች ሰንበትን የማክበር ግዴታ የለባቸውም። ቆላ 2:16, 17፤ ሮም 14:5, 10

ሰንበትንና የመሳሰሉትን በማክበራቸው ተወቅሰዋል። ገላ 4:9-11፤ ሮም 10:2-4

ወደ አምላክ እረፍት የምንገባው በእምነትና በታዛዥነት ነው። ዕብ 4:9-11

 ለ. ሰንበትን እንዲያከብሩ የታዘዙት የጥንት እስራኤላውያን ብቻ ናቸው

ሰንበት ለመጀመሪያ ጊዜ የተከበረው ከግብፅ ከወጡ በኋላ ነው። ዘፀ 16:26, 27, 29, 30

ለሥጋዊ እስራኤላውያን ብቻ ምልክት ሆኖ የሚያገለግል ነበር። ዘፀ 31:16, 17፤ መዝ 147:19, 20

ሕጉ ዓመታዊ ሰንበትንም ይጨምር ነበር። ዘፀ 23:10, 11፤ ዘሌ 25:3, 4

ሰንበት ለክርስቲያኖች አስፈላጊ ነገር አይደለም። ሮም 14:5, 10፤ ገላ 4:9-11

 ሐ. የአምላክ የሰንበት እረፍት (የፍጥረት “ሳምንት” 7ኛ ቀን)

ይህ ሰንበት የጀመረው ምድራዊ የፍጥረት ሥራ ሲያበቃ ነው። ዘፍ 2:2, 3፤ ዕብ 4:3-5

እረፍቱ ኢየሱስ ምድር ላይ ሳለና ከዚያ በኋላም ቀጥሏል። ዕብ 4:6-8፤ መዝ 95:7-9, 11

ክርስቲያኖች የግል ጥቅምን ለማስቀደም ከሚሠሩ ሥራዎች ያርፋሉ። ዕብ 4:9, 10

የአምላክ መንግሥት ከምድር ጋር በተያያዘ የሚያከናውነውን ሥራ ሲያጠናቅቅ የሰንበት እረፍት ያበቃል። 1ቆሮ 15:24, 28

19. ሲኦል (ሔዲስ)

  ሀ. ቃል በቃል እሳታማ የመሠቃያ ቦታ አይደለም

በሥቃይ ላይ የነበረው ኢዮብ እዚያ ለመሄድ ጸልዮአል። ኢዮብ 14:13

ምንም ዓይነት እንቅስቃሴ የማይካሄድበት ቦታ ነው። መዝ 6:5፤ መክ 9:10፤ ኢሳ 38:18, 19

ኢየሱስ ከመቃብር ወይም ከሲኦል ተነስቷል። ሥራ 2:27, 31, 32፤ መዝ 16:10

ሲኦል ሌሎቹን ሙታን ከሰጠ በኋላ ይጠፋል። ራእይ 20:13, 14

 ለ. እሳት የጥፋት ምሳሌ ነው

በሞት መጥፋት በእሳት ተመስሏል። ማቴ 25:41, 46፤ 13:30

ንስሐ የማይገቡ ክፉዎች ልክ በእሳት እንደጠፉ ያህል ለዘላለም ይጠፋሉ። ዕብ 10:26, 27

ሰይጣን በእሳት ‘እንደሚሠቃይ’ ተደርጎ መገለጹ ዘላለማዊ ሞትን ያመለክታል። ራእይ 20:10, 14, 15

 ሐ. የሀብታሙ ሰውና የአልዓዛር ታሪክ ዘላለማዊ ሥቃይ ለመኖሩ ማስረጃ አይደለም

የአብርሃም እቅፍ ምሳሌያዊ እንደሆነ ሁሉ እሳቱም ምሳሌያዊ ነው። ሉቃስ 16:22-24

በተጨማሪም የአብርሃምን ሞገስ ማግኘት ከጨለማ ጋር ተነጻጽሮ ተገልጿል። ማቴ 8:11, 12

በባቢሎን ላይ የሚደርሰው ጥፋት በእሳት እንደመሠቃየት ተደርጎ ተገልጿል። ራእይ 18:8-10, 21

20. በዓላት፣ የልደት ቀን

  ሀ. የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ልደትንና ገናን አያከብሩም ነበር

የእውነተኛ አምልኮ ተከታይ ያልሆኑ ሰዎች ልደትን አክብረዋል። ዘፍ 40:20፤ ማቴ 14:6

መከበር ያለበት ኢየሱስ የሞተበት ቀን ነው። ሉቃስ 22:19, 20፤ 1ቆሮ 11:25, 26

በበዓላት ቀን የሚታየው ፈንጠዝያ ተገቢ አይደለም። ሮም 13:13፤ ገላ 5:21፤ 1ጴጥ 4:3

21. ቤተ ክርስቲያን

  ሀ. ቤተ ክርስቲያን መንፈሳዊ ትርጉም አለው፣ የተገነባውም በክርስቶስ ላይ ነው

አምላክ ሰው በሠራው ቤተ መቅደስ አይኖርም። ሥራ 17:24, 25፤ 7:48

እውነተኛው ቤተ ክርስቲያን በሕያዋን ድንጋዮች የታነጸ መንፈሳዊ ቤተ መቅደስ ነው። 1ጴጥ 2:5, 6

ክርስቶስ የማዕዘን ድንጋይ ሲሆን ሐዋርያት ደግሞ በሁለተኛ ደረጃ ላይ የሚገኙ መሠረት ናቸው። ኤፌ 2:20

አምላክ መመለክ ያለበት በመንፈስና በእውነት ነው። ዮሐ 4:24

 ለ. ቤተ ክርስቲያን የተገነባው በጴጥሮስ ላይ አይደለም

ኢየሱስ፣ ቤተ ክርስቲያን በጴጥሮስ ላይ ይገነባል አላለም። ማቴ 16:18

ኢየሱስ “ዐለት” ተብሎ ተገልጿል። 1ቆሮ 10:4

ጴጥሮስ፣ ኢየሱስ መሠረት እንደሆነ ገልጿል። 1ጴጥ 2:4, 6-8፤ ሥራ 4:8-12

22. ቤዛ

  ሀ. የኢየሱስ ሰብዓዊ ሕይወት “ለሁሉም ቤዛ” ሆኖ ተከፍሏል

ኢየሱስ ሕይወቱን ቤዛ አድርጎ ሰጥቷል። ማቴ 20:28

የፈሰሰው ደም የኃጢአት ስርየት ያስገኛል። ዕብ 9:14, 22

አንዴ የተከፈለው መሥዋዕት ለሁልጊዜ በቂ ነው። ሮም 6:10፤ ዕብ 9:26

ጥቅሞቹ ወዲያው የሚመጡ አይደሉም፤ አምኖ መቀበል ያስፈልጋል። ዮሐ 3:16

 ለ. ተመጣጣኝ ዋጋ ነበር

አዳም ፍጹም ሆኖ ተፈጥሮ ነበር። ዘዳ 32:4፤ መክ 7:29፤ ዘፍ 1:31

ኃጢአት በመሥራቱ ራሱም ሆነ ልጆቹ ፍጽምናን አጡ። ሮም 5:12, 18

ልጆቹ ራሳቸውን ማዳን አልቻሉም፤ ከአዳም ጋር የሚመጣጠን አስፈለገ። መዝ 49:7፤ ዘዳ 19:21

የኢየሱስ ፍጹም ሰብዓዊ ሕይወት ቤዛ ሆነ። 1ጢሞ 2:5, 6፤ 1ጴጥ 1:18, 19

23. ተቃውሞ፣ ስደት

  ሀ. በክርስቲያኖች ላይ ተቃውሞ የሚደርስበት ምክንያት

ኢየሱስ ተጠልቷል፤ ተቃውሞ እንደሚመጣ አስቀድሞ ተናግሯል። ዮሐ 15:18-20፤ ማቴ 10:22

ትክክለኛ መሠረታዊ ሥርዓቶችን በጥብቅ መከተል ዓለምን ይኰንናል። 1ጴጥ 4:1, 4, 12, 13

የዚህ ሥርዓት አምላክ የሆነው ሰይጣን የአምላክን መንግሥት ይቃወማል። 2ቆሮ 4:4፤ 1ጴጥ 5:8

ክርስቲያን አይፈራም፤ አምላክ ይደግፈዋል። ሮም 8:38, 39፤ ያዕ 4:8

 ለ. ሚስት ባሏ ከአምላክ እንዲለያት መፍቀድ የለባትም

አስቀድሞ ማስጠንቀቂያ ተሰጥቷል፤ ሌሎች ያልሆነ ወሬ ሊነግሩት ይችላሉ። ማቴ 10:34-38፤ ሥራ 28:22

ከአምላክና ከክርስቶስ ጋር ያላትን ዝምድና አጥብቃ መያዝ አለባት። ዮሐ 6:68፤ 17:3

በታማኝነቷ እሱንም ማዳን ትችል ይሆናል። 1ቆሮ 7:16፤ 1ጴጥ 3:1-6

ባል ራስ ነው፤ ሆኖም የእሱን አምልኮ እንድትከተል ማስገደድ አይችልም። 1ቆሮ 11:3፤ ሥራ 5:29

 ሐ. ባል ሚስቱ አምላክን ማገልገሉን እንድታስተወው መፍቀድ የለበትም

ሚስቱንና ቤተሰቡን መውደድ አለበት፤ ሕይወት እንዲያገኙ ይፈልጋል። 1ቆሮ 7:16

ውሳኔ የማድረግና ለቤተሰቡ የሚያስፈልጉትን ነገሮች የማቅረብ ኃላፊነት አለበት። 1ቆሮ 11:3፤ 1ጢሞ 5:8

አምላክ ለእውነት የሚቆምን ሰው ይወዳል። ያዕ 1:12፤ 5:10, 11

ለሰላም ብሎ አቋምን ማላላት የአምላክን ሞገስ ያሳጣል። ዕብ 10:38

ቤተሰብህ በአዲሱ ዓለም ውስጥ የሚገኘው ደስታ ተካፋይ እንዲሆን እርዳ። ራእይ 21:3, 4

24. ትንሣኤ

  ሀ. የሙታን ተስፋ

በመቃብር ያሉት ሁሉ ይነሳሉ። ዮሐ 5:28, 29

የኢየሱስ ትንሣኤ ለዚህ ዋስትና ነው። 1ቆሮ 15:20-22፤ ሥራ 17:31

በመንፈስ ቅዱስ ላይ ኃጢአት የሠሩ አይነሱም። ማቴ 12:31, 32

እምነት የሚያሳዩ ትንሣኤ እንደሚያገኙ ዋስትና አላቸው። ዮሐ 11:25

 ለ. በሰማይ ወይም በምድር ላይ ለመኖር መነሳት

ሁሉም በአዳም ይሞታሉ፤ በኢየሱስ ሕይወት ያገኛሉ። 1ቆሮ 15:20-22፤ ሮም 5:19

የሚነሱት ሰዎች አካላዊ ሁኔታ ይለያያል። 1ቆሮ 15:40, 42, 44

ከኢየሱስ ጋር የሚሆኑት ልክ እንደ እሱ ይሆናሉ። 1ቆሮ 15:49፤ ፊልጵ 3:20, 21

ገዥ የማይሆኑት በምድር ላይ ይኖራሉ። ራእይ 20:4ለ, 5, 13፤ 21:3, 4

25. ኃጢአት

  ሀ. ኃጢአት ምንድን ነው?

የአምላክን ሕግ፣ እሱ ያወጣውን ፍጹም መሥፈርት መጣስ ማለት ነው። 1ዮሐ 3:4፤ 5:17

ሰው የአምላክ ፍጡር እንደመሆኑ በእሱ ዘንድ ተጠያቂ ነው። ሮም 14:12፤ 2:12-15

ሕጉ ኃጢአት ምን እንደሆነ ገለጸ፤ ሰዎች ኃጢአተኝነታቸው እንዲታወቃቸው አደረገ። ገላ 3:19፤ ሮም 3:20

ሁሉም ኃጢአት አለባቸው፤ የአምላክን ፍጹም መሥፈርት አያሟሉም። ሮም 3:23፤ መዝ 51:5

 ለ. ሁሉም በአዳም ኃጢአት አበሳ ያዩት ለምንድን ነው?

አዳም ለሁሉም አለፍጽምናንና ሞትን አስተላለፈ። ሮም 5:12, 18

አምላክ የሰው ልጆችን በመታገሥ መሐሪነቱን አሳይቷል። መዝ 103:8, 10, 14, 17

የኢየሱስ መሥዋዕት ኃጢአትን ያስተሰርያል። 1ዮሐ 2:2

ኃጢአትና ሌሎቹ የዲያብሎስ ሥራዎች በሙሉ ይወገዳሉ። 1ዮሐ 3:8

 ሐ. የተከለከለው ፍሬ ካለመታዘዝ ጋር እንጂ ከወሲብ ጋር ግንኙነት የለውም

ከዛፉ መብላት የተከለከለው ሔዋን ከመፈጠሯ በፊት ነው። ዘፍ 2:17, 18

አዳምና ሔዋን ልጆች እንዲወልዱ ተነግሯቸዋል። ዘፍ 1:28

ልጆች የአምላክ በረከት እንጂ የኃጢአት ውጤት አይደሉም። መዝ 127:3-5

ሔዋን ኃጢአት የሠራችው ባሏ በሌለበት ነው፤ ከእሱ ቀድማ ሄደች። ዘፍ 3:6፤ 1ጢሞ 2:11-14

ራሷ የነበረው አዳም በአምላክ ሕግ ላይ ዓመፀ። ሮም 5:12, 19

 መ. በመንፈስ ቅዱስ ላይ ኃጢአት መሥራት ሲባል ምን ማለት ነው? (ማቴ 12:32፤ ማር 3:28, 29)

ከአዳም የተወረሰው ኃጢአት ከዚህ የተለየ ነው። ሮም 5:8, 12, 18፤ 1ዮሐ 5:17

አንድ ሰው መንፈስን ሊያሳዝን ሆኖም ተስተካክሎ ወደ ቀድሞ ሁኔታው ሊመለስ ይችላል። ኤፌ 4:30፤ ያዕ 5:19, 20

ሆነ ብሎ ኃጢአት መሥራትን ልማድ ማድረግ ወደ ሞት ይመራል። 1ዮሐ 3:6-9

አምላክ እንደነዚህ ያሉትን ይፈርድባቸዋል፣ መንፈሱንም ይወስድባቸዋል። ዕብ 6:4-8

እንደነዚህ ላሉት ንስሐ የማይገቡ ሰዎች መጸለይ አይገባንም። 1ዮሐ 5:16, 17

26. ነፍስ

  ሀ. ነፍስ ምንድን ነች?

ሰው ነፍስ ነው። ዘፍ 2:7፤ 1ቆሮ 15:45፤ ኢያሱ 11:11 የ1954 ትርጉም፤ ሥራ 27:37

እንስሳትም ነፍሳት ተብለው ተጠርተዋል። ዘኁ 31:28 የ1879 ትርጉም፤ ራእይ 16:3ዘሌ 24:18 የ1879 ትርጉም

ነፍስ ደም አለው፣ ምግብ ይበላል፣ ሊሞት ይችላል። ኤር 2:34 የ1879 ትርጉም፤ መዝ 107:5, 9፤ ሕዝ 18:4

ሰው ሕይወት ስላለው ነፍስ አለው ሊባል ይችላል። ማር 8:36፤ ዮሐ 10:15

 ለ. በነፍስና በመንፈስ መካከል ያለው ልዩነት

ሕይወት ያለው ሰው ወይም ፍጡር ነፍስ ነው። ዮሐ 10:15፤ ዘሌ 17:11 የ1879 ትርጉም

ነፍሳትን የሚያንቀሳቅስ የሕይወት ኃይል “መንፈስ” ይባላል። መዝ 146:4፤ 104:29 NW

ሰው ሲሞት የሕይወት ኃይሉ እንደገና በአምላክ ቁጥጥር ሥር ይሆናል። መክ 12:7

የሕይወት ኃይልን መልሶ ሊሰጥ የሚችለው አምላክ ብቻ ነው። ሕዝ 37:12-14

27. አርማጌዶን

  ሀ. ክፋትን ለማስወገድ አምላክ የሚያደርገው ውጊያ

ብሔራት ወደ አርማጌዶን ይሰበሰባሉ። ራእይ 16:14, 16

አምላክ በልጁና በመላእክቱ አማካኝነት ይዋጋል። 2ተሰ 1:6-9፤ ራእይ 19:11-16

ከጥፋቱ መትረፍ የምንችለው እንዴት ነው? ሶፎ 2:2, 3፤ ራእይ 7:14

 ለ. እርምጃው የአምላክን ፍቅር አይጻረርም

ዓለም እጅግ ተበላሽቷል። 2ጢሞ 3:1-5

አምላክ ታጋሽ ነው፤ ቢሆንም ፍትሕ እርምጃ እንዲወሰድ ያስገድዳል። 2ጴጥ 3:9, 15፤ ሉቃስ 18:7, 8

ጻድቃን በጥሩ ሁኔታ መኖር እንዲችሉ ክፉዎች መጥፋት አለባቸው። ምሳሌ 21:18፤ ራእይ 11:18

28. አገልጋይ

  ሀ. ሁሉም ክርስቲያኖች አገልጋይ መሆን አለባቸው

ኢየሱስ የአምላክ አገልጋይ ነበር። ሮም 15:8, 9፤ ማቴ 20:28

ክርስቲያኖች የእሱን ምሳሌ ይከተላሉ። 1ጴጥ 2:21፤ 1ቆሮ 11:1

አገልግሎታቸውን ለማከናወን መስበክ ይኖርባቸዋል። 2ጢሞ 4:2, 5፤ 1ቆሮ 9:16

 ለ. ለአገልግሎት የሚያስፈልጉ ብቃቶች

የአምላክ መንፈስና የቃሉ እውቀት። 2ጢሞ 2:15፤ ኢሳ 61:1-3

ክርስቶስ በስብከቱ ሥራ የተወውን ምሳሌ ተከተሉ። 1ጴጥ 2:21፤ 2ጢሞ 4:2, 5

አምላክ በመንፈሱና በድርጅቱ በኩል ሥልጠና ይሰጣል። ዮሐ 14:26፤ 2ቆሮ 3:1-3

29. ኢየሱስ

  ሀ. ኢየሱስ የአምላክ ልጅና የተሾመ ንጉሥ ነው

የአምላክ የበኩር ልጅ ነው፤ ሁሉም ነገር የተፈጠረው በእሱ በኩል ነው። ራእይ 3:14፤ ቆላ 1:15-17

ከሴት የተወለደ፣ ከመላእክት ዝቅ ያለ ሰው ሆነ። ገላ 4:4፤ ዕብ 2:9

በአምላክ መንፈስ ተወለደ፤ የወደፊት ዕጣው ወደ ሰማይ መሄድ ነበር። ማቴ 3:16, 17

ሰው ከመሆኑ በፊት ከነበረው የበለጠ ክብር ተሰጠው። ፊልጵ 2:9, 10

 ለ. ለመዳን በኢየሱስ ክርስቶስ ማመን የግድ አስፈላጊ ነው

ክርስቶስ፣ እንደሚመጣ አስቀድሞ የተነገረለት የአብርሃም ዘር ነው። ዘፍ 22:18፤ ገላ 3:16

ብቸኛው ሊቀ ካህናት ኢየሱስ ነው፣ ቤዛ ሆኗል። 1ዮሐ 2:1, 2፤ ዕብ 7:25, 26፤ ማቴ 20:28

አምላክንና ክርስቶስን በማወቅና በመታዘዝ ሕይወት ይገኛል። ዮሐ 17:3፤ ሥራ 4:12

 ሐ. በኢየሱስ ከማመን የበለጠ ነገር ያስፈልጋል

እምነት በሥራ የተደገፈ መሆን አለበት። ያዕ 2:17-26፤ 1:22-25

ትእዛዛቱን ማክበርና እሱ የሠራውን ሥራ መሥራት አለብን። ዮሐ 14:12, 15፤ 1ዮሐ 2:3

ጌታ ብለው የሚጠሩት ሁሉ ወደ መንግሥቱ ይገባሉ ማለት አይደለም። ማቴ 7:21-23

30. ክፋት፣ በዓለም ላይ ያለው መከራ

  ሀ. በዓለም ላይ ላለው መከራ ተጠያቂው ማን ነው?

ዛሬ ላለው ክፉ ዘመን መንስኤው መጥፎ አገዛዝ ነው። ምሳሌ 29:2፤ 28:28

የዓለም ገዥ የአምላክ ጠላት ነው። 2ቆሮ 4:4፤ 1ዮሐ 5:19፤ ዮሐ 12:31

መከራ የመጣው በዲያብሎስ ነው፤ የቀረው ጊዜ አጭር ነው። ራእይ 12:9, 12

ዲያብሎስ ይታሰራል፤ ከዚያም ታላቅ ሰላም ይሰፍናል። ራእይ 20:1-3፤ 21:3, 4

 ለ. ክፋት እንዲኖር የተፈቀደው ለምንድን ነው?

ዲያብሎስ የአምላክ ፍጡሮች ከእሱ ጐን በታማኝነት አይቆሙም የሚል ክርክር አንስቷል። ኢዮብ 1:11, 12

ታማኝ ፍጡሮች ታማኝነታቸውን እንዲያስመሠክሩ አጋጣሚ ተሰጥቷቸዋል። ሮም 9:17፤ ምሳሌ 27:11

የዲያብሎስ ሐሰተኝነት ተረጋግጧል፤ የተነሳው ጥያቄ ሙሉ በሙሉ እልባት ያገኛል። ዮሐ 12:31

ታማኞቹ የዘላለም ሕይወት ሽልማት ያገኛሉ። ሮም 2:6, 7፤ ራእይ 21:3-5

 ሐ. የፍጻሜው ዘመን መርዘሙ የምሕረት ዝግጅት ነው

እንደ ኖኅ ዘመን ሁሉ ዛሬም ማስጠንቀቂያ ለመስጠት ጊዜ ያስፈልጋል። ማቴ 24:14, 37-39

አምላክ መሐሪ ነው እንጂ እርምጃ ለመውሰድ አይዘገይም። 2ጴጥ 3:9፤ ኢሳ 30:18

መጽሐፍ ቅዱስ ሳናስበው በወጥመድ ከመያዝ እንድንጠበቅ ይረዳናል። ሉቃስ 21:36፤ 1ተሰ 5:4

ጥበቃ ለማግኘት አሁኑኑ አምላክ ባዘጋጀው ዝግጅት ተጠቀሙ። ኢሳ 2:2-4፤ ሶፎ 2:3

 መ. በዓለም ላይ ላለው መከራ ሰው መፍትሔ ሊያመጣ አይችልም

ሰዎች በፍርሃት ተውጠዋል፣ ግራ ተጋብተዋል። ሉቃስ 21:10, 11፤ 2ጢሞ 3:1-5

የሚሳካለት የአምላክ መንግሥት እንጂ የሰዎች መንግሥት አይደለም። ዳን 2:44፤ ማቴ 6:10

በሕይወት ለመኖር ከንጉሡ ጋር አሁኑኑ ሰላም መሥርቱ። መዝ 2:9, 11, 12

31. ዕድል ተወስኗል?

  ሀ. የሰው ዕድል አስቀድሞ አልተወሰነም

የአምላክ ዓላማ መፈጸሙ የተረጋገጠ ነው። ኢሳ 55:11፤ ዘፍ 1:28

ግለሰቦች አምላክን ለማገልገል ምርጫ ተሰጥቷቸዋል። ዮሐ 3:16፤ ፊልጵ 2:12

32. የመጨረሻዎቹ ቀኖች

  ሀ. “የዓለም ፍጻሜ” ሲባል ምን ማለት ነው?

የዚህ ሥርዓት መደምደሚያ ማለት ነው። ማቴ 24:3፤ 2ጴጥ 3:5-7፤ ማር 13:14

የክፉ ሥርዓት እንጂ የምድር ፍጻሜ አይደለም። 1ዮሐ 2:17

ከጥፋቱ በፊት የፍጻሜ ዘመን መምጣት አለበት። ማቴ 24:14

ጻድቃን ይድናሉ፤ አዲስ ሥርዓት ይከተላል። 2ጴጥ 2:9፤ ራእይ 7:14-17

 ለ. የመጨረሻውን ቀን ምልክቶች ነቅቶ መከታተል ያስፈልጋል

አምላክ ጊዜውን ለይተን እንድናውቅ ምልክቶች ሰጥቶናል። 2ጢሞ 3:1-5፤ 1ተሰ 5:1-4

ዓለም የጉዳዩን አሳሳቢነት መገንዘብ ተስኖታል። 2ጴጥ 3:3, 4, 7፤ ማቴ 24:39

አምላክ እርምጃ ለመውሰድ አይዘገይም፤ ነገር ግን ማስጠንቀቂያ ይሰጣል። 2ጴጥ 3:9

ሁኔታውን በንቃትና በትኩረት መከታተል ወሮታ ያስገኛል። ሉቃስ 21:34-36

33. የቀድሞ አባቶችን ማምለክ

  ሀ. የቀድሞ አባቶችን ማምለክ ከንቱ ነው

የቀድሞ አባቶች ሙት ናቸው፣ ምንም አያውቁም። መክ 9:5, 10

የመጀመሪያዎቹ ወላጆች መመለክ የሚገባቸው አይደሉም። ሮም 5:12, 14፤ 1ጢሞ 2:14

አምላክ ይህን ዓይነቱን አምልኮ ይከለክላል። ዘፀ 34:14፤ ማቴ 4:10

 ለ. ሰዎች ሊከበሩ ይችላሉ፤ መመለክ የሚገባው ግን አምላክ ብቻ ነው

ወጣቶች ትልልቅ ሰዎችን ማክበር አለባቸው። 1ጢሞ 5:1, 2, 17፤ ኤፌ 6:1-3

መመለክ የሚገባው ግን አምላክ ብቻ ነው። ሥራ 10:25, 26፤ ራእይ 22:8, 9

34. የክርስቶስ መመለስ

  ሀ. መመለሱ በሰው ዓይን አይታይም

ወደፊት ዓለም እንደማያየው ለደቀ መዛሙርቱ ነግሯቸዋል። ዮሐ 14:19

ማረጉን የተመለከቱት ደቀ መዛሙርቱ ብቻ ናቸው፤ የሚመለሰውም በተመሳሳይ ሁኔታ ነው። ሥራ 1:6, 10, 11

የማይታይ መንፈስ ሆኖ በሰማይ ይኖራል። 1ጢሞ 6:14-16፤ ዕብ 1:3

የአምላክ መንግሥት ንጉሥ ሆኖ ይመለሳል። ዳን 7:13, 14

 ለ. መመለሱን የሚያሳዩ በዓይን የሚታዩ ነገሮች

ደቀ መዛሙርቱ የመገኘቱን ምልክት እንዲነግራቸው ጠይቀውት ነበር። ማቴ 24:3

ክርስቲያኖች መገኘቱን “የሚያዩት” በማስተዋል ዓይናቸው ነው። ኤፌ 1:18

የመገኘቱ ማስረጃ የሆኑ ብዙ ክንውኖች አሉ። ሉቃስ 21:10, 11

ጠላቶች ጥፋት ሲመጣባቸው “ያዩታል።” ራእይ 1:7

35. የዘመናት ስሌት

  ሀ. የአሕዛብ ዘመን በ1914 (ከክ. ል. በኋላ) ተፈጸመ

የነገሥታቱ ሥርወ መንግሥት በ607 ከክ. ል. በፊት ተቋረጠ። ሕዝ 21:25-27

አገዛዙ ዳግም እስኪቋቋም ድረስ “ሰባት ዓመት” ማለፍ ነበረበት። ዳን 4:32, 16, 17

ሰባት = 2 × 3 1/2 ዓመት፤ ወይም 2 × 1,260 ቀናት። ራእይ 12:6, 14፤ 11:2, 3

አንድ ቀን እንደ አንድ ዓመት ተደርጎ ይወሰዳል። [2,520 ዓመታት ይሆናሉ።] ሕዝ 4:6፤ ዘኁ 14:34

ይህ የአሕዛብ ዘመን መንግሥቱ እስኪቋቋም ድረስ የሚቀጥል ነበር። ሉቃስ 21:24፤ ዳን 7:13, 14

36. የይሖዋ ምሥክሮች

  ሀ. የይሖዋ ምሥክሮች አመጣጥ

ይሖዋ የራሱን ምሥክሮች ማንነት ገልጿል። ኢሳ 43:10-12፤ ኤር 15:16

ከአቤል አንስቶ ብዙ ታማኝ ምሥክሮች አሉት። ዕብ 11:4, 39፤ 12:1

ኢየሱስ የታመነና እውነተኛ ምሥክር ነው። ዮሐ 18:37፤ ራእይ 1:5፤ 3:14

37. ይሖዋ፣ አምላክ

  ሀ. የአምላክ ስም

“አምላክ” የሚለው ቃል የወል ስም ነው፣ ጌታችን የግል ስም አለው። 1ቆሮ 8:5, 6

ስሙ እንዲቀደስ እንጸልያለን። ማቴ 6:9, 10

የአምላክ ስም ይሖዋ ነው። መዝ 83:18 NW፤ ዘፀ 6:2, 3 የ1879 ትርጉም፤ 3:15 NW፤ ኢሳ 42:8 NW

በኪንግ ጄምስ ትርጉም ስሙ ዘፀ 6:3 ላይ ይገኛል (ዲዋይ የግርጌ ማስታወሻ)። መዝ 83:18 NW፤ ኢሳ 12:2 NW፤ 26:4 NW

ኢየሱስ ይህን ስም ለሰዎች አሳውቋል። ዮሐ 17:6, 26፤ 5:43፤ 12:12, 13, 28

 ለ. የአምላክ መኖር

አምላክን አይቶ መኖር አይቻልም። ዘፀ 33:20፤ ዮሐ 1:18፤ 1ዮሐ 4:12

ለማመን አምላክን ማየት አያስፈልግም። ዕብ 11:1፤ ሮም 8:24, 25፤ 10:17

አምላክ በሚታዩ ሥራዎቹ ይታወቃል። ሮም 1:20፤ መዝ 19:1, 2

የትንቢቶች መፈጸም የአምላክን መኖር ያረጋግጣል። ኢሳ 46:8-11

 ሐ. የአምላክ ባሕርያት

አምላክ ፍቅር ነው። 1ዮሐ 4:8, 16፤ ዘፀ 34:6፤ 2ቆሮ 13:11፤ ሚክ 7:18 [NW]

በጥበብ የላቀ ነው። ኢዮብ 12:13፤ ሮም 11:33፤ 1ቆሮ 2:7

ፍትሐዊ ነው፤ ፍትሕ እንዲሰፍን ያደርጋል። ዘዳ 32:4፤ መዝ 37:28

ሁሉን ቻይ ነው፤ ኃይሉ ገደብ የለውም። ኢዮብ 37:23፤ ራእይ 7:12፤ 4:11

 መ. ሁሉም ሰው የሚያመልከው አንዱን አምላክ አይደለም

ጥሩ የሚመስል መንገድ ሁሉ ትክክለኛ ነው ማለት አይደለም። ምሳሌ 16:25፤ ማቴ 7:21

ሁለት መንገዶች አሉ፤ ወደ ሕይወት የሚመራው አንዱ ብቻ ነው። ማቴ 7:13, 14፤ ዘዳ 30:19

ብዙ አማልክት አሉ፤ እውነተኛው አምላክ ግን አንድ ነው። 1ቆሮ 8:5, 6፤ መዝ 82:1

እውነተኛውን አምላክ ማወቅ ሕይወት ለማግኘት የግድ አስፈላጊ ነው። ዮሐ 17:3፤ 1ዮሐ 5:20

38. ደም

  ሀ. ደም መውሰድ ወይም መስጠት ከደም ቅድስና ጋር ይቃረናል

ኖኅ ደም ቅዱስ እንደሆነና ሕይወት እንደሆነ ተነግሮት ነበር። ዘፍ 9:4, 16

የሕጉ ቃል ኪዳን ደም መብላትን ይከለክል ነበር። ዘሌ 17:14፤ 7:26, 27

ክርስቲያኖችም ከደም እንዲርቁ ታዘዋል። ሥራ 15:28, 29፤ 21:25

 ለ. ሕይወትን ለማዳን ነው የሚለው ሰበብ የአምላክን ሕግ ለማፍረስ ምክንያት ሊሆን አይችልም

መታዘዝ ከመሥዋዕት ይበልጣል። 1ሳሙ 15:22፤ ማር 12:33

የራስን ሕይወት ከአምላክ ሕግ ማስቀደም ለሞት ይዳርጋል። ማር 8:35, 36

39. ዲያብሎስ፣ አጋንንት

  ሀ. ዲያብሎስ መንፈሳዊ አካል ነው

በሰው ውስጥ ያለ ክፋት ሳይሆን መንፈሳዊ አካል ነው። 2ጢሞ 2:26

ዲያብሎስ ልክ እንደ መላእክት ራሱን የቻለ አንድ አካል ነው። ማቴ 4:1, 11፤ ኢዮብ 1:6

በውስጡ መጥፎ ምኞቶችን በማሳደር ራሱን ዲያብሎስ አደረገ። ያዕ 1:13-15

 ለ. ዲያብሎስ በዓይን የማይታይ የዓለም ገዥ ነው

እንደ አምላክ ሆኖ ዓለምን ይቆጣጠራል። 2ቆሮ 4:4፤ 1ዮሐ 5:19፤ ራእይ 12:9

ክርክሩ መልስ እስኪያገኝ ድረስ እንዲቆይ ተፈቀደለት። ዘፀ 9:16፤ ዮሐ 12:31

በጥልቅ ውስጥ ይታሰራል፤ ከዚያም ይደመሰሳል። ራእይ 20:2, 3, 10

 ሐ. አጋንንት ዓመፀኛ መላእክት ናቸው

ከጥፋት ውኃ በፊት ከሰይጣን ጎን ተሰለፉ። ዘፍ 6:1, 2፤ 1ጴጥ 3:19, 20

እንዲዋረዱ ተደርገዋል፤ ማንኛውም የእውቀት ብርሃን ተቋርጦባቸዋል። 2ጴጥ 2:4፤ ይሁዳ 6

አምላክን ይጻረራሉ፤ ሰውን ይጨቁናሉ። ሉቃስ 8:27-29፤ ራእይ 16:13, 14

ከሰይጣን ጋር ይደመሰሳሉ። ማቴ 25:41፤ ሉቃስ 8:31፤ ራእይ 20:2, 3, 10

40. ጋብቻ

  ሀ. ጋብቻ በክብር መያዝ አለበት

ከክርስቶስና ከሙሽራው ጋር ተመሳስሏል። ኤፌ 5:22, 23

የጋብቻ መኝታ መርከስ የለበትም። ዕብ 13:4

ባልና ሚስት ተለያይተው እንዳይኖሩ ተመክረዋል። 1ቆሮ 7:10-16

ለፍቺ የሚያበቃው ቅዱስ ጽሑፋዊ መሠረት ፖርኒያ ብቻ ነው። ማቴ 19:9

 ለ. ክርስቲያኖች የራስነትን መሠረታዊ ሥርዓት ማክበር አለባቸው

ባል ራስ እንደመሆኑ መጠን ቤተሰቡን መውደድና መንከባከብ አለበት። ኤፌ 5:23-31

ሚስት ለባሏ መገዛት፣ እሱን ማፍቀርና መታዘዝ አለባት። 1ጴጥ 3:1-7፤ ኤፌ 5:22

ልጆች ታዛዥ መሆን አለባቸው። ኤፌ 6:1-3፤ ቆላ 3:20

 ሐ. ክርስቲያን ወላጆች ልጆቻቸውን በተመለከተ ያለባቸው ኃላፊነት

ጊዜያቸውንና ተገቢውን ትኩረት በመስጠት ፍቅር ማሳየት አለባቸው። ቲቶ 2:4

አታበሳጯቸው። ቆላ 3:21

መንፈሳዊ ነገሮችን ጨምሮ የሚያስፈልጓቸውን ነገሮች አሟሉላቸው። 2ቆሮ 12:14፤ 1ጢሞ 5:8

ሕይወታቸውን እንዴት መምራት እንዳለባቸው አሠልጥኗቸው። ኤፌ 6:4፤ ምሳሌ 22:6, 15፤ 23:13, 14

 መ. ክርስቲያኖች ማግባት ያለባቸው ክርስቲያኖችን ብቻ ነው

ማግባት ያለባችሁ “በጌታ ብቻ” ነው። 1ቆሮ 7:39፤ ዘዳ 7:3, 4፤ ነህ 13:26

 . ከአንድ በላይ ማግባት ቅዱስ ጽሑፋዊ ድጋፍ የለውም

በመጀመሪያ የነበረው ዝግጅት አንድ ሰው አንዲት ሚስት ብቻ እንድትኖረው ነበር። ዘፍ 2:18, 22-25

ኢየሱስ ክርስቲያኖች ይህንኑ መሥፈርት እንዲከተሉ አስተምሯል። ማቴ 19:3-9

የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ከአንድ በላይ አያገቡም ነበር። 1ቆሮ 7:2, 12-16፤ ኤፌ 5:28-31

41. ጥምቀት

  ሀ. ክርስቲያኖች ሊያሟሉት የሚገባ ብቃት

ኢየሱስ ምሳሌ ትቶልናል። ማቴ 3:13-15፤ ዕብ 10:7

ራሳችንን መካዳችንን ወይም ለአምላክ መወሰናችንን የሚያሳይ ምልክት ነው። ማቴ 16:24፤ 1ጴጥ 3:21

መማር የሚችሉበት ዕድሜ ላይ የደረሱ ብቻ ይጠመቃሉ። ማቴ 28:19, 20፤ ሥራ 2:41

ትክክለኛው መንገድ ውኃ ውስጥ ማጥለቅ ነው። ሥራ 8:38, 39፤ ዮሐ 3:23

 ለ. ኃጢአትን አጥቦ አያስወግድም

ኢየሱስ የተጠመቀው ከኃጢአት ታጥቦ ለመንጻት አልነበረም። 1ጴጥ 2:22፤ 3:18

ኃጢአትን የሚያጥበው የኢየሱስ ደም ነው። 1ዮሐ 1:7

42. ጸሎት

  ሀ. አምላክ የሚሰማቸው ጸሎቶች

አምላክ የሰዎችን ጸሎት ይሰማል። መዝ 145:18፤ 1ጴጥ 3:12

ዓመፀኞች አካሄዳቸውን ካልለወጡ ተሰሚነት አያገኙም። ኢሳ 1:15-17

በኢየሱስ ስም መጸለይ ያስፈልጋል። ዮሐ 14:13, 14፤ 2ቆሮ 1:20

ከአምላክ ፈቃድ ጋር የሚስማማ ጸሎት ማቅረብ አለብን። 1ዮሐ 5:14, 15

እምነት አስፈላጊ ነው። ያዕ 1:6-8

 ለ. በከንቱ መደጋገም፣ ለማርያም ወይም “ለቅዱሳን” መጸለይ ዋጋ የለውም

በኢየሱስ ስም ወደ አምላክ መጸለይ አለብን። ዮሐ 14:6, 14፤ 16:23, 24

እንዲሁ ቃላትን መደጋገም ተሰሚነት አያስገኝም። ማቴ 6:7

43. ፈውስ፣ ልሳን

  ሀ. መንፈሳዊ ፈውስ ዘላቂ ጥቅሞች አሉት

መንፈሳዊ ሕመም ለጥፋት ይዳርጋል። ኢሳ 1:4-6፤ 6:10፤ ሆሴዕ 4:6

ዋነኛው ተልእኮ መንፈሳዊ ፈውስ ነው። ዮሐ 6:63፤ ሉቃስ 4:18

ኃጢአትን ያስወግዳል፤ ደስታና ሕይወት ይሰጣል። ያዕ 5:19, 20፤ ራእይ 7:14-17

 ለ. የአምላክ መንግሥት ዘላቂ አካላዊ ፈውስ ያመጣል

ኢየሱስ የተለያዩ በሽታዎችን ፈውሷል፤ መንግሥቱ ስለሚያመጣቸው በረከቶችም ሰብኳል። ማቴ 4:23

መንግሥቱ ዘላቂ ፈውስ እንደሚያስገኝ ተስፋ ተሰጥቷል። ማቴ 6:10፤ ኢሳ 9:7

ሞትም እንኳ ይጠፋል። 1ቆሮ 15:25, 26፤ ራእይ 21:4፤ 20:14

 ሐ. በዘመናችን ተአምራዊ ፈውስ መለኮታዊ ድጋፍ ያለው ለመሆኑ ማስረጃ የለም

ደቀ መዛሙርት ራሳቸውን በተአምር አይፈውሱም ነበር። 2ቆሮ 12:7-9፤ 1ጢሞ 5:23

ተአምር የማድረግ ስጦታዎች ከሐዋርያት ዘመን በኋላ አቁመዋል። 1ቆሮ 13:8-11

መፈወስ የአምላክ ድጋፍ ለመኖሩ አስተማማኝ ማስረጃ አይደለም። ማቴ 7:22, 23፤ 2ተሰ 2:9-11

 መ. በልሳን መናገር ለጊዜው ብቻ የተሰጠ ስጦታ ነበር

ምልክት ብቻ ነበር፤ ክርስቲያኖች ከዚያ የሚበልጡትን ስጦታዎች መፈለግ ነበረባቸው። 1ቆሮ 14:22፤ 12:30, 31

የመንፈስ ተአምራዊ ስጦታዎች እንደሚቀሩ አስቀድሞ ተነግሮ ነበር። 1ቆሮ 13:8-10

የተለያዩ ድንቅ ነገሮችን መፈጸም የአምላክ ድጋፍ መኖሩን የሚያሳይ አስተማማኝ ማስረጃ አይደለም። ማቴ 7:22, 23፤ 24:24

44. ፍጥረት

  ሀ. በትክክለኛ ማስረጃ ከተደገፈ ሳይንስ ጋር ይስማማል፤ የዝግመተ ለውጥን ጽንሰ ሐሳብ ውድቅ ያደርጋል

ሳይንስ ከፍጥረት ሥራ ቅደም ተከተል ጋር ይስማማል። ዘፍ 1:11, 12, 21, 24, 25

አምላክ ሁሉም ‘እንደየወገኑ’ እንዲባዛ ያወጣው ሕግ እውነት ሆኖ ተገኝቷል። ዘፍ 1:11, 12፤ ያዕ 3:12

 ለ. የፍጥረት ቀናት የ24 ሰዓት ርዝመት ያላቸው ቀናት አይደሉም

“ቀን” አንድን የተወሰነ ጊዜ ሊያመለክት ይችላል። ዘፍ 2:4 የ1954 ትርጉም

በአምላክ ዘንድ ቀን ረጅም ዘመንን ሊያመለክት ይችላል። መዝ 90:4፤ 2ጴጥ 3:8