በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ጥናት 16

አዎንታዊና የሚያበረታታ

አዎንታዊና የሚያበረታታ

ኢዮብ 16:5

ፍሬ ሐሳብ፦ በችግሮች ላይ ሳይሆን በመፍትሔያቸው ላይ ትኩረት አድርግ፤ አድማጮችህን ለተግባር የሚያነሳሱ ነጥቦችን ጥቀስ።

ይህን ማድረግ የምትችለው እንዴት ነው?

  • ስለ አድማጮችህ አዎንታዊ አመለካከት ይኑርህ። ወንድሞችህና እህቶችህ ይሖዋን ማስደሰት እንደሚፈልጉ እምነት ሊኖርህ ይገባል። አንዳንድ ጊዜ ምክር መስጠት ሊያስፈልግህ ይችላል፤ ያም ሆኖ ተገቢ በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ፣ ምክር ከመስጠትህ በፊት አመስግናቸው።

  • ብዙ ችግር አታውራ። አንድን ችግር የምትጠቅሰው ለንግግርህ ጠቃሚ ሆኖ ካገኘኸው ብቻ ሊሆን ይገባል። የንግግርህ አጠቃላይ መንፈስ የሚያበረታታ መሆን ይኖርበታል።

  • የአምላክን ቃል በሚገባ ተጠቀምበት። ይሖዋ ለሰው ልጆች ያደረገውን፣ አሁን እያደረገ ያለውንና ወደፊት የሚያደርገውን ነገር አበክረህ ግለጽ። ንግግርህ አድማጮችህን የሚያበረታታና ተስፋ የሚፈነጥቅላቸው ሊሆን ይገባል።