በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ክፍል 11

በእርግጥ ይሖዋ ይሰማናል?

በእርግጥ ይሖዋ ይሰማናል?

አምላክ ጸሎታችንን ይሰማል። 1 ጴጥሮስ 3:12

ይሖዋ “ጸሎት ሰሚ” አምላክ ነው። (መዝሙር 65:2) የልባችንን አውጥተን እንድንነግረው ይፈልጋል።

መጸለይ ያለብን ወደ ይሖዋ ብቻ ነው።

ስለተለያዩ ጉዳዮች መጸለይ እንችላለን። 1 ዮሐንስ 5:14

የአምላክ ፈቃድ በሰማይና በምድር እንዲፈጸም ጸልይ።

ኢየሱስ ያደረገልህን ነገር ከፍ አድርገህ እንደምትመለከት ለማሳየት በእሱ ስም ጸልይ።

መልካም የሆነውን ነገር እንድታደርግ እንዲረዳህ ይሖዋን ለምነው። በተጨማሪም ስለ ምግብ፣ ስለ ሥራ፣ ስለ መጠለያ፣ ስለ ልብስና ስለ ጤንነት መጸለይ ትችላለህ።