“ተከታዬ ሁን”

የዚህ መጽሐፍ ዓላማ የኢየሱስን ሕይወትና አገልግሎት ሙሉ በሙሉ መከለስ ሳይሆን እሱን መከተል የሚቻልበትን መንገድ በግልጽ ማስተዋል እንድንችል መርዳት ነው።

መቅድም

ለኢየሱስ ያለህ ፍቅር እንዲያድግ እንዲሁም የእሱን ፈለግ በጥብቅ በመከተል አሁንም ሆነ ለዘላለም የይሖዋን ልብ ደስ ማሰኘት እንድትችል ልባዊ ምኞታችን ነው።

ምዕራፍ 1

“ተከታዬ ሁን”—ኢየሱስ ምን ማለቱ ነበር?

እውነተኛ የኢየሱስ ተከታይ መሆን ከምንናገረው ነገር አሊያም ለእሱ ካለን ስሜት የበለጠ ነገርን ያካትታል።

ምዕራፍ 2

“መንገድ፣ እውነትና ሕይወት”

ወደ አብ መቅረብ የሚቻለው በልጁ በኩል ብቻ ነው። ኢየሱስ፣ አምላክ ለአጽናፈ ዓለሙ ያለውን ዓላማ በማስፈጸም ረገድ ወሳኝ የሆነ ቦታ ተሰጥቶታል።

ምዕራፍ 3

“እኔ . . . በልቤ ትሑት ነኝ”

ኢየሱስ በምድር ላይ አገልግሎቱን ባከናወነበት ጊዜ ሁሉ ትሕትና አሳይቷል።

ምዕራፍ 4

“እነሆ፣ ከይሁዳ ነገድ የሆነው አንበሳ”

ኢየሱስ በሦስት መንገዶች እንደ አንበሳ ዓይነት ድፍረት አሳይቷል፦ ለእውነት ጥብቅና በመቆም፣ ለፍትሕ በመቆርቆርና ተቃውሞን በመጋፈጥ።

ምዕራፍ 5

“የጥበብ . . . ውድ ሀብት ሁሉ”

ኢየሱስ ንግግሩ ብቻ ሳይሆን ተግባሩም የላቀ ጥበብ የሚንጸባረቅበት ነበር።

ምዕራፍ 6

“መታዘዝን ተማረ”

ኢየሱስ ለአባቱ ፍጹም ታዛዥ ነበር፤ ታዲያ “መታዘዝን ተማረ” እና ‘ፍጹም ሆነ’ ሊባል የሚችለው እንዴት ነው?

ምዕራፍ 7

“በጽናት የተቋቋመውን እሱን በጥሞና አስቡ”

ኢየሱስ በጽናት ረገድ እንከን የለሽ ታሪክ አስመዝግቧል። ለመጽናት የረዳው ምንድን ነው? የእሱን የጽናት ምሳሌ መከተል የምንችለው እንዴት ነው?

ምዕራፍ 8

“የተላክሁት ለዚህ ዓላማ ነው”

ኢየሱስ ምድር ላይ በነበረበት ወቅት የሰበከው ለምን እንደሆነ፣ ስለ ምን እንደሰበከና ስለተሰጠው ሥራ ምን አመለካከት እንደነበረው እንድታነብ እንጋብዝሃለን።

ምዕራፍ 9

“ሂዱና . . . ደቀ መዛሙርት አድርጉ”

ኢየሱስ ደቀ መዛሙርት እንድናደርግ የሰጠው ተልእኮ የእውነተኛ የክርስቶስ ተከታይ ዓይነተኛ መገለጫ ነው።

ምዕራፍ 10

“ተብሎ ተጽፏል”

ከአምላክ ቃል መጥቀስ፣ ለቃሉ ጥብቅና መቆምና ቃሉን ማብራራት እውነትን ለሌሎች በማካፈል ረገድ የኢየሱስን ምሳሌ የምንከተልባቸው ቁልፍ መንገዶች ናቸው።

ምዕራፍ 11

“ማንም ሰው እንደዚህ ተናግሮ አያውቅም”

ኢየሱስ ከተጠቀመባቸው የማስተማሪያ ዘዴዎች መካከል ሦስቱን እንዲሁም እነዚህን ዘዴዎች እንዴት መኮረጅ እንደምንችል እንድትመረምር እንጋብዝሃለን።

ምዕራፍ 12

“ያለምሳሌ አይነግራቸውም ነበር”

መጽሐፍ ቅዱስ፣ ኢየሱስ ምሳሌዎችን ለመጠቀም የመረጠበትን ሁለት ዋነኛ ምክንያቶች ይገልጽልናል።

ምዕራፍ 13

‘እኔ አብን እወደዋለሁ’

እንደ ኢየሱስ ለአምላክ ጥልቅ ፍቅር ማዳበር የምንችለው እንዴት ነው?

ምዕራፍ 14

‘እጅግ ብዙ ሰዎች ወደ እሱ መጡ’

ልጆችን ጨምሮ በጣም ብዙ ሰዎች ወደ ኢየሱስ መቅረብ አልከበዳቸውም። ኢየሱስ ይህን ያህል የሚቀረብ ሰው እንዲሆን ያስቻለው ምንድን ነው?

ምዕራፍ 15

“በጣም አዘነላቸው”

ለሌሎች ምሕረት ወይም ርኅራኄ በማሳየት ረገድ የኢየሱስን ምሳሌ መከተላችን አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

ምዕራፍ 16

“ኢየሱስ . . . እስከ መጨረሻው ወደዳቸው”

ኢየሱስ አገልግሎቱን ባከናወነባቸው ጊዜያት ሁሉ ለደቀ መዛሙርቱ ያለውን ፍቅር በተለያዩ መንገዶች አሳይቷል። እኛስ ከሌሎች ጋር ባለን ግንኙነት እንደ ኢየሱስ ዓይነት ፍቅር ማሳየት የምንችለው እንዴት ነው?

ምዕራፍ 17

‘ከዚህ የበለጠ ፍቅር ያለው ማንም የለም’

እንደ ኢየሱስ የራስን ጥቅም የመሠዋት መንፈስ የሚንጸባረቅበት ፍቅር ማሳየት የምንችለው እንዴት ነው?

ምዕራፍ 18

“እኔን መከተልህን ቀጥል”

ኢየሱስን በየዕለቱ ከተከተልነው ንጹሕ ሕሊናና ብሩህ የወደፊት ተስፋ ይኖረናል።