በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

በምርጫ የሚሰጡ ሹመቶች

በምርጫ የሚሰጡ ሹመቶች

በምርጫ የሚሰጡ ሹመቶች

በብዙ ትምህርት ቤቶች ተማሪዎች በድምጽ ብልጫ ተመርጠው እንደ ክፍል አለቃ ወይም ፕሬዘዳንት የመሰለ ሹመት ይሰጣቸዋል። አንዳንድ ትምህርት ቤቶች አነስተኛ የፖለቲካ ዘመቻ ያካሂዳሉ። በተጨማሪም ዕጩዎችን የሚያስተዋውቁባቸው ፖስተሮችና ተለጣፊ ወረቀቶች ያዘጋጃሉ። ዓላማውም ወጣቶችን ከፖለቲካ አሠራር ጋር ለማስተዋወቅ ነው። ይሁን እንጂ ምሥክር ወጣቶች ራሳቸውን ለምርጫ በማቅረብም ሆነ ሌሎችን በመምረጥ በትምህርት ቤት በሚከናወነው ፖለቲካ አይካፈሉም። ስለዚህ ለተወዳዳሪነት ቢሰየሙ ወይም ለሥልጣን ቢመረጡ ጥበብ በተሞላበት መንገድ እንደማይቀበሉ ያስታውቃሉ። በዚህ መንገድ ሊያነግሡት ሲፈልጉ የሸሸውን የኢየሱስን ምሳሌ ይከተላሉ።—ዮሐንስ 6:15

ይሁን እንጂ መምህሩ ራሱ ሲመድብ ሁኔታው የተለየ ይሆናል። ስለዚህ ምሥክሮች ለትራፊክ አመራር ወይም ይህን ለሚመስል ሥራ እንዲረዱ በመምህራቸው ቢመረጡ በተቻላቸው ሁሉ እንዲተባበሩ ይበረታታሉ።

በእርግጥ ወጣቶቻችን ሁሉም ዓይነት ምርጫ ፖለቲካዊ አለመሆኑን ይገነዘባሉ። አንዳንዴ ተማሪዎች በተወሰነ ጉዳይ ላይ አስተያየት እንዲሰጡ መምህሩ ሊጠይቃቸው ይችላል። ስለ አንዳንድ ሥራዎች ወይም እንቅስቃሴዎች የሚሰማቸውን እንዲናገሩ ወይም ለአንድ ንግግር ወይም ድርሰት ያላቸውን አስተያየት እንዲገልጹ ቢጠየቁ የመጽሐፍ ቅዱስን መሠረታዊ ሥርዓቶች መጣስ ላይሆንባቸው ይችላል። ስለ አንዳንድ ነገሮች ጥሩነት ያላቸውን አስተያየት ለመግለጽ እጅ ማውጣትና አንድን ሰው ለፖለቲካዊ ሥልጣን ለመምረጥ እጅ ማውጣት የተለያዩ ነገሮች ናቸው።

[በገጽ 23 ላይ የሚገኝ ሥዕል]

ምሥክር ወጣቶች በትምህርት ቤት በሚከናወነው ፖለቲካ አይካፈሉም