በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ሣጥን 9ሠ

“ነገሮች ሁሉ የሚታደሱበት ዘመን”

“ነገሮች ሁሉ የሚታደሱበት ዘመን”

የሐዋርያት ሥራ 3:21

ሐዋርያው ጴጥሮስ “ነገሮች ሁሉ የሚታደሱበት ዘመን” ሲል ክርስቶስ ከነገሠበት ጊዜ አንስቶ እስከ ሺው ዓመት ማብቂያ ድረስ ስለሚዘልቅ አስደናቂ ዘመን በትንቢት መናገሩ ነበር።

  1. 1914​—ኢየሱስ ክርስቶስ በሰማይ ንጉሥ ሆኖ መግዛት ጀመረ። የአምላክን ሕዝቦች በመንፈሳዊ ሁኔታ መልሶ የማቋቋሙ ሥራ በ1919 ጀመረ

    የመጨረሻዎቹ ቀናት

  2. አርማጌዶን​—የክርስቶስ የሺህ ዓመት ግዛት ይጀምራል፤ ‘ነገሮች ሁሉ በሚታደሱበት ዘመን’ ውስጥ በሚካተተው በዚህ ወቅት ምድር ቃል በቃል ትታደሳለች፤ በምድር ላይ የሚኖሩ ታማኝ የሰው ልጆችም ሥጋዊ በረከቶችን ያገኛሉ

    የሺህ ዓመት ግዛት

  3. የሺው ዓመት ግዛት ፍጻሜ​—ኢየሱስ የማደሱን ወይም መልሶ የማቋቋሙን ሥራ አጠናቅቆ መንግሥቱን ለአባቱ ያስረክባል

    ዘላለማዊ ገነት

በኢየሱስ አገዛዝ ሥር . . .

  • የአምላክ ስም ክብር ይጎናጸፋል

  • የታመሙ ጤንነታቸው ይመለሳል

  • አረጋውያን ወደ ወጣትነት ይመለሳሉ

  • ሙታን ዳግመኛ ሕያው ይሆናሉ

  • ታማኝ የሰው ልጆች ፍጹም ይሆናሉ

  • ምድር ገነት ትሆናለች