ሣጥን 13ሀ
የተለያዩ ቤተ መቅደሶች፣ የተለያዩ ትምህርቶች
ሕዝቅኤል በራእይ ያየው ቤተ መቅደስ፦
-
ሕዝቅኤል በባቢሎን ለነበሩ አይሁዳውያን ግዞተኞች ስለዚህ ቤተ መቅደስ ተናግሯል
-
ብዙ መሥዋዕቶች የሚቀርቡበት መሠዊያ አለው
-
ይሖዋ ለንጹሕ አምልኮ ያወጣውን መሥፈርት ጎላ አድርጎ ይገልጻል
-
ትኩረታችን በ1919 በጀመረው መንፈሳዊ ተሃድሶ ላይ እንዲያርፍ ያደርጋል
ታላቁ መንፈሳዊ ቤተ መቅደስ፦
-
ጳውሎስ ለዕብራውያን ክርስቲያኖች በጻፈው ደብዳቤ ላይ አብራርቶታል
-
አንድ መሥዋዕት ብቻ “ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ” የቀረበበት መሠዊያ አለው (ዕብ. 10:10)
-
የማደሪያ ድንኳኑና ሌሎቹ ቤተ መቅደሶች ጥላ የሆኑለትን መንፈሳዊ እውነታ ማለትም ይሖዋ በክርስቶስ ቤዛዊ መሥዋዕት አማካኝነት ለንጹሕ አምልኮ ያደረገውን ዝግጅት ያመለክታል
-
ትኩረታችን ክርስቶስ ታላቅ ሊቀ ካህናት በመሆን ከ29 እስከ 33 ዓ.ም. ባከናወነው ሥራ ላይ እንዲያርፍ ያደርጋል