በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ክፍል ሦስት

‘እሰበስባችኋለሁ’—ንጹሕ አምልኮ መልሶ እንደሚቋቋም በትንቢት ተነገረ

‘እሰበስባችኋለሁ’—ንጹሕ አምልኮ መልሶ እንደሚቋቋም በትንቢት ተነገረ

ሕዝቅኤል 20:41

ፍሬ ሐሳብ፦ በሕዝቅኤል ትንቢት ውስጥ የሚገኙ ንጹሕ አምልኮ መልሶ እንደሚቋቋም የሚገልጹ ተስፋዎች

በእስራኤል ውስጥ ክህደት ስለተስፋፋ አንድነቷ ክፉኛ ተናግቷል። እስራኤል ንጹሕ አምልኮን ያረከሰች ከመሆኑም ሌላ የአምላክን ስም አጉድፋለች፤ ስለዚህ ድርጊቷ ያስከተለባትን መዘዝ እየተቀበለች ነው። እንዲህ ባለው ተስፋ አስቆራጭ ሁኔታ ውስጥ ይሖዋ ሕዝቅኤልን ተስፋ ሰጪ የሆኑ ትንቢቶችን እንዲናገር አነሳሳው። ይሖዋ ምስል ከሳች የሆኑ አገላለጾችንና አስደናቂ ራእዮችን በመጠቀም በግዞት ያሉትን እስራኤላውያን ብቻ ሳይሆን ንጹሕ አምልኮ መልሶ ሲቋቋም ማየት የሚናፍቁትን ሁሉ የሚያጽናና ሐሳብ አስነግሯል።

በዚህ ክፍል ውስጥ

ምዕራፍ 8

“አንድ እረኛ . . . አስነሳለሁ”

ይሖዋ ሕዝቅኤልን በመንፈሱ በመምራት ስለ መሲሑ ማለትም ንጹሕ አምልኮን ለአንዴና ለመጨረሻ ጊዜ መልሶ ስለሚያቋቁመው እረኛና ገዢ ትንቢት እንዲናገር አድርጓል።

ምዕራፍ 9

“አንድ ልብ እሰጣቸዋለሁ”

በባቢሎን ለሚኖሩት ታማኝ አይሁዳውያን ግዞተኞች የተነገሩት ትንቢቶች ለእኛም የያዙት መልእክት አለ?

ምዕራፍ 10

“ሕያው ትሆናላችሁ”

ሕዝቅኤል በአንድ ሸለቆ ውስጥ የተከመሩ የደረቁ አጥንቶች ሕያው ሲሆኑ በራእይ አየ። የራእዩ ትርጉም ምንድን ነው?

ምዕራፍ 11

“ጠባቂ አድርጌ ሾሜሃለሁ”

ይህ ጠባቂ ያለው ኃላፊነት ምንድን ነው? ምን ዓይነት ማስጠንቀቂያ ማወጅ ነበረበት?

ምዕራፍ 12

“አንድ ብሔር አደርጋቸዋለሁ”

ይሖዋ ሕዝቦቹን አንድ እንደሚያደርግ ተስፋ ሰጠ።

ምዕራፍ 13

“ስለ ቤተ መቅደሱ ግለጽላቸው”

ሕዝቅኤል በራእይ ያየው ቤተ መቅደስ ትርጉም ምንድን ነው?

ምዕራፍ 14

“የቤተ መቅደሱ ሕግ ይህ ነው”

በግዞት የነበሩት አይሁዳውያን ሕዝቅኤል ስለ ቤተ መቅደሱ ካየው ራእይ ምን ትምህርት አግኝተው መሆን አለበት? ይህ ራእይ እኛንስ ምን ያስተምረናል?