የክፍል 12 ማስተዋወቂያ
ኢየሱስ ለሰዎች ስለ መንግሥተ ሰማያት አስተምሯል። እንዲሁም የአምላክ ስም እንዲቀደስ፣ መንግሥቱ እንዲመጣና ፈቃዱ በምድር ላይ እንዲፈጸም እንዲጸልዩ አስተምሯቸዋል። ወላጅ ከሆንክ ልጅህ ይህ ጸሎት ለእኛ ምን ትርጉም እንዳለው እንዲገነዘብ እርዳው። ኢየሱስ በሰይጣን ፈተና ተሸንፎ ታማኝነቱን አላጓደለም። ከጊዜ በኋላ ሐዋርያቱን መረጠ፤ እነሱም የአምላክ መንግሥት የመጀመሪያ አባላት ከመሆናቸውም ሌላ በመንግሥቱ ውስጥ ትልቅ ሚና ይጫወታሉ። ኢየሱስ ለእውነተኛው አምልኮ ከፍተኛ ቅንዓት አሳይቷል። ሰዎችን የመርዳት ፍላጎት ስለነበረው የታመሙትን ፈውሷል፤ የተራቡትን መግቧል፤ እንዲሁም የሞቱትን አስነስቷል። እነዚህን ተአምራት በመፈጸም የአምላክ መንግሥት ለሰው ልጆች ምን በረከት እንደሚያመጣ አሳይቷል።
በዚህ ክፍል ውስጥ
ትምህርት 77
ውኃ ልትቀዳ የመጣችው ሳምራዊት ሴት
አንዲት ሳምራዊት ሴት ኢየሱስ ሲያነጋግራት በጣም ተገረመች። ለምን? ኢየሱስ ለሌላ ለማንም ሰው ያልተናገረውን ምን ነገር ነገራት?
ትምህርት 78
ኢየሱስ የአምላክን መንግሥት ምሥራች ሰበከ
ኢየሱስ አንዳንድ ደቀ መዛሙርቱን “ሰው አጥማጆች” እንዲሆኑ ጥሪ አቀረበላቸው። ከጊዜ በኋላም ከተከታዮቹ መካከል 70ዎቹን ምሥራቹን እንዲሰብኩ አሠለጠናቸው።
ትምህርት 79
ኢየሱስ ብዙ ተአምራት ፈጽሟል
ኢየሱስ በሄደበት ቦታ ሁሉ፣ የታመሙ ሰዎች ከበሽታቸው እንዲያድናቸው ወደ እሱ ይመጡ ነበር፤ እሱም ሁሉንም ፈውሷቸዋል። አንዲትን የሞተች ልጅ እንኳ አስነስቷል።