በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የክፍል 3 ማስተዋወቂያ

የክፍል 3 ማስተዋወቂያ

መጽሐፍ ቅዱስ ከጥፋት ውኃው በኋላ ባሉት ዓመታት ውስጥ ይሖዋን ያገለግሉ የነበሩ ጥቂት ሰዎችን ይጠቅሳል። ከእነዚህ ሰዎች መካከል የይሖዋ ወዳጅ ተብሎ የተጠራው አብርሃም ይገኝበታል። አብርሃም የይሖዋ ወዳጅ የተባለው ለምንድን ነው? ወላጅ ከሆንክ ልጅህን ይሖዋ በግለሰብ ደረጃ እንደሚያስብለትና ሊረዳው እንደሚፈልግ እንዲገነዘብ እርዳው። ልክ እንደ አብርሃም፣ እንደ ሎጥና እንደ ያዕቆብ ሁሉ እኛም ይሖዋ እንዲረዳን በነፃነት ልንጠይቀው እንችላለን። ይሖዋ ቃል የገባውን ነገር በሙሉ እንደሚፈጽም እርግጠኛ መሆን እንችላለን።

በዚህ ክፍል ውስጥ

ትምህርት 7

የባቤል ግንብ

አንዳንድ ሰዎች ከተማ ለመገንባትና ሰማይ የሚደርስ ግንብ ለመሥራት አስበው ነበር። ይሖዋ የተለያየ ቋንቋ እንዲናገሩ ያደረጋቸው ለምንድን ነው?

ትምህርት 8

አብርሃምና ሣራ አምላክን ታዘዋል

አብርሃምና ሣራ በዑር ከተማ የነበራቸውን ሕይወት ትተው በከነአን ምድር ከቦታ ቦታ እየተዘዋወሩ ለመኖር ፈቃደኛ የሆኑት ለምንድን ነው?

ትምህርት 9

በመጨረሻ ልጅ ወለዱ!

አምላክ ለአብርሃም የገባለትን ቃል የሚፈጽመው እንዴት ነው? ቃሉ የሚፈጸመው በይስሐቅ በኩል ነው ወይስ በእስማኤል?

ትምህርት 10

የሎጥን ሚስት አስታውሱ

አምላክ በሰዶምና በገሞራ ላይ እሳትና ድኝ አዘነበ። እነዚህ ከተሞች የጠፉት ለምንድን ነው? የሎጥን ሚስት ማስታወስ ያለብን ለምንድን ነው?

ትምህርት 11

የአብርሃም እምነት ተፈተነ

አምላክ አብርሃምን ‘እባክህ አንድ ልጅህን ወስደህ በሞሪያ ምድር በሚገኝ ተራራ ላይ መሥዋዕት አድርገህ አቅርበው’ አለው። አብርሃም ይህን የእምነት ፈተና እንዴት ይወጣው ይሆን?

ትምህርት 12

ያዕቆብ ውርስ አገኘ

ይስሐቅና ርብቃ፣ ኤሳውና ያዕቆብ የሚባሉ መንታ ልጆች ነበሯቸው። መጀመሪያ የተወለደው ኤሳው ስለነበር ለየት ያለ ውርስ የሚያገኘው እሱ ነበር። ለአንድ ሳህን ወጥ ሲል ይህን ውርስ አሳልፎ የሰጠው ለምንድን ነው?

ትምህርት 13

ያዕቆብና ኤሳው ታረቁ

ያዕቆብ በረከት ያገኘው እንዴት ነው? ከኤሳው ጋር የታረቀውስ እንዴት ነው?