በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ትምህርት 9

የአምላክ ወዳጆች እነማን ናቸው?

የአምላክ ወዳጆች እነማን ናቸው?

ኢየሱስ ክርስቶስ የይሖዋ ልጅ፣ እንዲሁም የቅርብ ወዳጁ ነው። ኢየሱስ ሰው ሆኖ ምድር ላይ ከመኖሩ በፊት ኃያል መንፈሳዊ ፍጡር ሆኖ በሰማይ ይኖር ነበር። (ዮሐንስ 17:5) ከዚያም ስለ አምላክ እውነትን ለሰዎች ለማስተማር ወደ ምድር መጣ። (ዮሐንስ 18:37) በተጨማሪም ታዛዥ ሰዎችን ከኃጢአትና ከሞት ለማዳን ሰብዓዊ ሕይወቱን ሰጥቷል። (ሮሜ 6:23) ኢየሱስ አሁን የአምላክ መንግሥት ንጉሥ ሲሆን በዚህ ሰማያዊ መስተዳድር አማካኝነት ምድርን ገነት ያደርጋል።—ራእይ 19:16

መላእክትም የአምላክ ወዳጆች ናቸው። መላእክት ሕልውናቸውን ያገኙት እንደ ሰው በምድር ላይ አይደለም። አምላክ ምድርን ከመፍጠሩ በፊት እነሱ በሰማይ ተፈጥረው ነበር። (ኢዮብ 38:4-7) መላእክት በሚልዮን የሚቆጠሩ ናቸው። (ዳንኤል 7:10) እነዚህ በሰማይ የሚኖሩ የአምላክ ወዳጆች ሰዎች ስለ ይሖዋ እውነቱን እንዲማሩ ይፈልጋሉ።—ራእይ 14:6, 7

በተጨማሪም አምላክ በምድር ላይ ወዳጆች አሉት፤ ምሥክሮቼ በማለት ይጠራቸዋል። በፍርድ ቤት የሚቀርብ አንድ ምሥክር ስለ አንድ ሰው ወይም ነገር የሚያውቀውን ይናገራል። የይሖዋ ምሥክሮች ስለ ይሖዋና ስለ ዓላማው የሚያውቁትን ሁሉ ለሰዎች ይናገራሉ። (ኢሳይያስ 43:10) እንደ መላእክት ሁሉ ምሥክሮቹም ስለ ይሖዋ እውነቱን እንድታውቅ ሊረዱህ ይፈልጋሉ። አንተም የአምላክ ወዳጅ እንድትሆን ይፈልጋሉ።