የ2017 የክልል ስብሰባ ፕሮግራም

መልካም የሆነውን ማድረግህን እንድትቀጥልና ፈተናዎችን መቋቋም እንድትችል እንዲረዳህ ተብሎ በተዘጋጀው በዚህ የክልል ስብሰባ እያንዳንዱ ቀን ላይ የሚቀርቡትን ክፍሎች ተመልከት።

ዓርብ

ክርስቲያኖች ፈተናዎችን በጽናት ለመቋቋም የሚያስፈልጉትን ባሕርያት ማዳበር እንዲችሉ ምን ሊረዳቸው ይችላል?

ቅዳሜ

ሁሉን ቻይ የሆነው አምላክ ጽናትና ማጽናኛ የሚሰጠን እንዴት ነው?

እሁድ

ኢየሱስ “እስከ መጨረሻው የጸና . . . ይድናል” በማለት ተናግሯል። እስከ መጨረሻው ለመጽናት ምን ማድረግ ይኖርብሃል?

ለተሰብሳቢዎች የቀረበ መረጃ

በፕሮግራሙ ላይ በሚደረጉ ለየት ያሉ ስብሰባዎች ላይ መገኘት ትፈልግ ይሆናል። በተጨማሪም አስተናጋጆችን፣ ጥምቀትን፣ መዋጮዎችን፣ የመጀመሪያ ደረጃ የሕክምና እርዳታን፣ ጠፍተው የተገኙ ዕቃዎች የሚቀመጡበትን ቦታ አሊያም ፈቃደኛ አገልግሎትን በተመለከተ ይበልጥ ማወቅ ከፈለግክ በዚህ ሥር መመልከት ትችላለህ።