በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ማኅበራዊ ልዩነቶች

ማኅበራዊ ልዩነቶች

ዘራችን፣ ከትልቅ ቤተሰብ መወለዳችን ወይም የኢኮኖሚ ደረጃችን በአምላክ ዘንድ ላቅ ያለ ቦታ ያሰጠናል?

ሥራ 17:26, 27፤ ሮም 3:23-27፤ ገላ 2:6፤ 3:28

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዮሐ 8:31-40—አንዳንድ አይሁዳውያን አባታቸው አብርሃም እንደሆነ በመግለጽ ይኩራሩ ነበር፤ ኢየሱስ ግን ድርጊታቸው ከአብርሃም ፈጽሞ የተለየ እንደሆነ በመግለጽ አስተሳሰባቸው የተሳሳተ መሆኑን ነግሯቸዋል

ሰዎችን በዘራቸው ወይም በአገራቸው የተነሳ ዝቅ አድርገን የምንመለከትበት ምክንያት ይኖራል?

ዮሐ 3:16፤ ሮም 2:11

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዮናስ 4:1-11—ነቢዩ ዮናስ የሌላ አገር ሕዝቦች ለሆኑት የነነዌ ሰዎች ምሕረት እንዲያሳይ ይሖዋ በትዕግሥት አስተምሮታል

    • ሥራ 10:1-8, 24-29, 34, 35—ሐዋርያው ጴጥሮስ አሕዛብን ርኩስ አድርጎ መመልከት እንደሌለበት ተምሯል፤ በመሆኑም ቆርኔሌዎስንና ቤተሰቡን ክርስቲያኖች እንዲሆኑ ረድቷቸዋል፤ እነዚህ ሰዎች ካልተገረዙ አሕዛብ ወገን የሆኑ የመጀመሪያዎቹ ክርስቲያኖች ናቸው

ሀብታም የሆኑ ክርስቲያኖች ከሌሎች እንደሚበልጡ ሊያስቡ ወይም ከሌሎች የተለየ ነገር እንዲደረግላቸው ሊጠብቁ ይገባል?

1ጢሞ 6:17, 18፤ ያዕ 2:2-4

በተጨማሪም ዘዳ 8:12-14፤ ኤር 9:23, 24⁠ን ተመልከት

የበላይ ተመልካችነት ኃላፊነት አንድን ሰው ከሌሎች ያስበልጠዋል? ሌሎችን እንዳሻው ለማዘዝስ መብት ይሰጠዋል?

2ቆሮ 1:24፤ 1ጴጥ 5:2, 3

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዘዳ 17:18-20—ይሖዋ፣ የእስራኤል ነገሥታት ራሳቸውን ከወገኖቻቸው ከፍ አድርገው መመልከት እንደሌለባቸው አስጠንቅቋል፤ ተገዢዎቻቸውን እንደ ወንድሞቻቸው አድርገው ማየት ይጠበቅባቸው ነበር

    • ማር 10:35-45—ሐዋርያቱ ሥልጣንና ክብር ከልክ በላይ ያሳስባቸው የነበረ በመሆኑ ኢየሱስ አርሟቸዋል። (በእንግሊዝኛው አዲስ ዓለም ትርጉም፣ ማር 10:42 ላይ “ሥልጣናቸውን እንደሚያሳዩ” ለሚለው ሐሳብ የተዘጋጀውን ለጥናት የሚረዳ መረጃ ተመልከት)

አንድን ሰው በአምላክ ዘንድ ተቀባይነት የሚያስገኝለት ነገር ምንድን ነው?

ክርስቲያኖች ማኅበራዊ ለውጥ ለማምጣት በሚደረጉ ንቅናቄዎች መካፈል ይኖርባቸዋል?

ኤፌ 6:5-9፤ 1ጢሞ 6:1, 2

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • ዮሐ 6:14, 15—ሕዝቡ ኢየሱስ ማኅበራዊ ለውጥ እንደሚያመጣ ጠብቀው ሊሆን ይችላል፤ ኢየሱስ ግን እንዲያነግሡት አልፈለገም