አምልኮ
ሊመለክ የሚገባው ማን ብቻ ነው?
-
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
-
ማቴ 4:8-10—ሰይጣን፣ ኢየሱስ አንድ ጊዜ ካመለከው የዓለምን መንግሥታት ሁሉ እንደሚሰጠው ቃል ገባለት፤ ኢየሱስ ግን ግብዣውን አልተቀበለም፤ መመለክ ያለበት ይሖዋ ብቻ እንደሆነ ተናገረ
-
ራእይ 19:9, 10—አንድ ኃያል መልአክ፣ ሐዋርያው ዮሐንስ አምልኮ አከል ክብር እንዲሰጠው አልፈቀደለትም
-
ይሖዋ እንድናመልከው የሚፈልገው እንዴት ነው?
-
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
-
ኢሳ 1:10-17—ይሖዋ፣ የእሱን መሥፈርቶች ለመከተል አሻፈረኝ ያሉ ግብዝ ሰዎች የሚያቀርቡለትን የአምልኮ ሥርዓቶች አይቀበልም እንዲሁም ይጸየፋቸዋል
-
ማቴ 15:1-11—ይሖዋ በወግ ላይ የተመሠረተ አምልኮን እንደማይቀበል ኢየሱስ ተናግሯል፤ ምክንያቱም እንዲህ ያለው አምልኮ ሰዎች ያወጧቸውን ደንቦች ከአምላክ ሕጎች ያስቀድማል
-
የሚቻል በሚሆንበት ጊዜ ሁሉ ይሖዋን ማምለክ ያለብን ከማን ጋር ነው?
በተጨማሪም መዝ 133:1-3ን ተመልከት
-
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
-
ሥራ 2:40-42—በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበሩ ክርስቲያኖች ለጸሎት፣ አብረው ጊዜ ለማሳለፍና በመንፈስ መሪነት የተጻፉ ትምህርቶችን አብረው ለማጥናት ይሰበሰቡ ነበር
-
1ቆሮ 14:26-40—ሐዋርያው ጳውሎስ የጉባኤ ስብሰባዎች ሥርዓታማና የሚያንጹ እንዲሆኑ መመሪያ ሰጥቷል፤ ዓላማውም ስብሰባው ላይ የተገኙት ሁሉ እንዲማሩና የሚተላለፈውን ትምህርት እንዲረዱ ነው
-
አምልኳችን በይሖዋ ዘንድ ተቀባይነት እንዲያገኝ ምን ማድረግ አለብን?
-
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
-
ዕብ 11:6—ሐዋርያው ጳውሎስ ይሖዋን ተቀባይነት ባለው መንገድ ለማምለክ እምነት የግድ አስፈላጊ መሆኑን ገልጿል
-
ያዕ 2:14-17, 24-26—የኢየሱስ ወንድም የሆነው ያዕቆብ፣ እምነታችን በሥራ የተደገፈ መሆን እንዳለበት ተናግሯል፤ ለተግባር የሚያነሳሳን እምነታችን ነው
-