እምነት
ይሖዋ ለእምነት ትልቅ ቦታ እንደሚሰጥ እንዴት እናውቃለን?
ዮሐ 3:16, 18፤ ገላ 3:8, 9, 11፤ ኤፌ 6:16፤ ዕብ 11:6
በተጨማሪም 2ቆሮ 5:7ን ተመልከት
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
ዕብ 11:1–12:3—ሐዋርያው ጳውሎስ ለእምነት ፍቺ ሰጥቷል፤ እንዲሁም ከአቤል አንስቶ እስከ ኢየሱስ ክርስቶስ ድረስ ብዙ የእምነት ምሳሌዎችን ጠቅሷል
ያዕ 2:18-24—ያዕቆብ እምነታችን በተግባር የተደገፈ መሆን እንዳለበት ለማሳየት የአብርሃምን ምሳሌ ጠቅሷል
እምነታችንን ለማጠናከር ምን ይረዳናል?
ሮም 10:9, 10, 17፤ 1ቆሮ 16:13፤ ያዕ 2:17
በተጨማሪም ዕብ 3:12-14ን ተመልከት
ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦
2ዜና 20:1-6, 12, 13, 20-23—የአምላክ ሕዝቦች ኃያል ጠላት ሲመጣባቸው ንጉሥ ኢዮሳፍጥ በይሖዋና በነቢያቱ እንዲያምኑ፣ እንዲህ ካደረጉም እንደሚሳካላቸው ነገራቸው
1ነገ 18:41-46—ነቢዩ ኤልያስ ለረጅም ጊዜ የዘለቀው ድርቅ እንደሚያበቃ ይሖዋ የገባውን ቃል ፍጻሜ በትዕግሥት ጠብቋል፤ በዚህም እምነት አሳይቷል