በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የጠበቅነው ሳይሆን ሲቀር

የጠበቅነው ሳይሆን ሲቀር

ሌሎች እንደጠበቅናቸው ሳይሆኑ ሲቀሩ፣ ሲጎዱን ይባስ ብሎም ሲከዱን

መዝ 55:12-14፤ ሉቃስ 22:21, 48

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • 1ሳሙ 8:1-6—ነቢዩ ሳሙኤል፣ እስራኤላውያን መጥተው ንጉሥ ካላነገሥክልን ሲሉት ቅር ተሰኝቷል

    • 1ሳሙ 20:30-34—ዮናታን፣ አባቱ ንጉሥ ሳኦል በቁጣ በመናገር ስላዋረደው ስሜቱ ተጎድቷል

  • የሚያጽናኑ ጥቅሶች፦

  • የሚያጽናኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • መዝ 55:12-14, 16-18, 22—ንጉሥ ዳዊት የቅርብ ወዳጁ የሆነው አኪጦፌል ቢከዳውም ሸክሙን በይሖዋ ላይ ጥሏል፤ ይህም አጽናንቶታል

    • 2ጢሞ 4:16-18—ሐዋርያው ጳውሎስ ፈተና ውስጥ ሳለ አንዳንዶች ትተውት ሄደዋል፤ ሆኖም ይሖዋ ኃይል ሰጥቶታል፤ ተስፋውም አበርትቶታል

በራሳችን ድክመት ወይም ኃጢአት የተነሳ፣ የጠበቅነው ሳይሆን ሲቀር

ኢዮብ 14:4፤ ሮም 3:23፤ 5:12

  • ጠቃሚ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • መዝ 51:1-5—ንጉሥ ዳዊት በይሖዋ ላይ በፈጸመው ኃጢአት የተነሳ፣ በበደለኝነት ስሜት ተደቁሷል

    • ሮም 7:19-24—ሐዋርያው ጳውሎስ ከኃጢአት ዝንባሌ ጋር በሚያደርገው የማያባራ ትግል የተነሳ ከንቱነት ተሰምቶታል

  • የሚያጽናኑ ጥቅሶች፦

  • የሚያጽናኑ የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች፦

    • 1ነገ 9:2-5—ንጉሥ ዳዊት ከባድ ኃጢአቶች ቢሠራም ይሖዋ የሚያስታውሰው በንጹሕ አቋም ጠባቂነቱ ነው

    • 1ጢሞ 1:12-16—ሐዋርያው ጳውሎስ በቀድሞ ሕይወቱ አስከፊ ነገሮች ቢያደርግም ምሕረት እንደሚያገኝ ተማምኗል