በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

የመጽሐፍ ቅዱስ አገላለጽ

“በቀደሙት ዘመናት የተፈጸሙትን ኃጢአቶች ይቅር ብሏል”

“በቀደሙት ዘመናት የተፈጸሙትን ኃጢአቶች ይቅር ብሏል”

ለኃጢአታችን ይቅርታ ማግኘት የምንችለው ኢየሱስ በደሙ በከፈለው ቤዛዊ መሥዋዕት አማካኝነት ብቻ ነው። (ኤፌ. 1:7) ይሁንና መጽሐፍ ቅዱስ “አምላክ ቻይ በመሆን በቀደሙት ዘመናት [ማለትም ኢየሱስ ቤዛውን ከመክፈሉ በፊት] የተፈጸሙትን ኃጢአቶች ይቅር ብሏል” ይላል። (ሮም 3:25) ይሖዋ ፍጹም የሆነውን የፍትሕ መሥፈርቱን ሳይጥስ ይህን ማድረግ የቻለው እንዴት ነው?

ይሖዋ እምነት ያላቸውን የሰው ልጆች የሚያድን “ዘር” እንደሚያዘጋጅ ከወሰነበት ቅጽበት አንስቶ በእሱ ዓይን ቤዛው እንደተከፈለ ሊቆጠር ይችላል። (ዘፍ. 3:15፤ 22:18) አምላክ፣ ጊዜው ሲደርስ አንድያ ልጁ ቤዛውን በፈቃደኝነት እንደሚከፍል ሙሉ በሙሉ እርግጠኛ ነበር። (ገላ. 4:4፤ ዕብ. 10:7-10) ኢየሱስ የአምላክ ወኪል ሆኖ በምድር ላይ በኖረበት ወቅት ገና ቤዛው ባይከፈልም እንኳ የሰዎችን ኃጢአት ይቅር የማለት ሥልጣን ነበረው። ይህን ያደረገው፣ ወደፊት የሚከፈለው ቤዛ እምነት ያላቸውን ሰዎች ኃጢአት እንደሚሸፍን ስላወቀ ነው።—ማቴ. 9:2-6