በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

መልስህ ምንድን ነው?

መልስህ ምንድን ነው?

መልስህ ምንድን ነው?

ምሳሌውን አብራራ

1. በማቴዎስ 18:12-14 ላይ ተመዝግቦ በሚገኘው የኢየሱስ ምሳሌ ላይ አንዱ በግ ምን ሆነ?

․․․․․․

2. እረኛ ምንድን ነው?

․․․․․․

3. እረኛው የጠፋውን በግ በማግኘቱ ምን ተሰማው?

․․․․․․

▪ ለውይይት:- ይሖዋ ከእረኛ ጋር የሚመሳሰለው በምን መንገድ ነው? አንተስ ከበግ ጋር የምትመሳሰለው እንዴት ነው?

ዘመኑ መቼ ነበር?

ከታች የተዘረዘሩትን የመጽሐፍ ቅዱስ መጻሕፍት የጻፉትን ሰዎች ስም ጻፍ። ከዚያም መጽሐፉን ተጽፎ እንዳለቀ ከሚገመትበት ዘመን ጋር በመስመር አገናኝ።

455 ከክ.ል.በፊት ከ443 ከክ.ል.በፊት ቆየት ብሎ ከ62 ከክ.ል.በኋላ ቀደም ብሎ 64 ከክ.ል.በኋላ ከ70 ከክ.ል.በኋላ ቆየት ብሎ

4. ሚልክያስ

5. ያዕቆብ

6. 2 ጴጥሮስ

እኔ ማን ነኝ?

7. ያዕቆብ፣ መልእክት ይዘው የመጡ ሰዎችን እንግድነት በመቀበሌ እንደጸደቅሁ ተናግሯል።

እኔ ማን ነኝ?

8. ለበርናባስ የአክስቱ ልጅ ስሆን ጴጥሮስ ደግሞ ልጄ ብሎ ጠርቶኛል።

ከዚህ እትም

የሚከተሉትን ጥያቄዎች መልስ፤ እንዲሁም የጎደለውን ቁጥር አሟላ።

ገጽ 8 ኢዮብ ስለ ምድር ምን ተናግሯል? (ኢዮብ 26:․․․)

ገጽ 11 የጥንቶቹ ክርስቲያኖች ቅዱሳን መጻሕፍትን እንዴት ይመለከቷቸው ነበር? (1 ተሰሎንቄ 2:․․․)

ገጽ 12 የእስራኤል ነገሥታት ምን እንዲጽፉ ተነግሯቸው ነበር? (ዘዳግም 17:․․․)

ገጽ 28 መጽሐፍ ቅዱስ ስለ ምን ነገር ፈትነህ እንድታውቅ ምክር ይሰጥሃል? (ሮሜ 12:․․․)

ለልጆች የቀረበ የሥዕል ጥያቄ

ከዚህ መጽሔት ውስጥ እነዚህን ሥዕሎች ማግኘት ትችላለህ? እያንዳንዱ ሥዕል ምን እንደሚያሳይ በራስህ አባባል ግለጽ።

(መልሱ በገጽ 27 ላይ ይገኛል)

በገጽ 31 ላይ ለቀረቡት ጥያቄዎች የተሰጡ መልሶች

1. ጠፋ።

2. በጎችን የሚጠብቅና የሚንከባከብ ሰው።

3. ደስ አለው።

4. ሚልክያስ፣ ከ443 ከክ.ል.በፊት ቆየት ብሎ

5. ያዕቆብ፣ ከ62 ከክ.ል.በኋላ ቀደም ብሎ

6. ጴጥሮስ፣ 64 ከክ.ል.በኋላ

7. ረዓብ።—ያዕቆብ 2:25

8. ማርቆስ።—ቈላስይስ 4:10፤ 1 ጴጥሮስ 5:13