በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

መልስህ ምንድን ነው?

መልስህ ምንድን ነው?

መልስህ ምንድን ነው?

ይህ የሆነው የት ነበር?

1. ኢየሱስ አልፎ የተሰጠበት ቦታ የት ነው?

ፍንጭ:- ማቴዎስ 26:36-56ን አንብብ።

መልስህን በካርታው ላይ አክብብ።

ጌቴሴማኒ የአትክልት ሥፍራ

ቤተ መቅደስ

የገዥው ግቢ

የሰሊሆም መጠመቂያ

▪ ከሐዋርያቱ መካከል ኢየሱስን አሳልፎ የሰጠው ማን ነው?

․․․․․

▪ በሊቀ ካህናቱ አገልጋይ ላይ ጥቃት የሰነዘረው ሐዋርያ ማን ነው?

․․․․․

ለውይይት:-

ኢየሱስ፣ አንድ የእሱ ተከታይ በጦር መሣሪያ አማካኝነት ሊያስጥለው ሲሞክር ምን አለው? ኢየሱስ፣ ለደቀ መዛሙርቱ ከተናገረው ነገር ምን ትምህርት አገኘህ?

ከዚህ እትም

የሚከተሉትን ጥያቄዎች መልስ፤ እንዲሁም የጎደለውን ቁጥር አሟላ።

ገጽ 3 ኢየሱስ እንደተናገረው እሱ የተወለደው ምን ለማድረግ ነበር? ዮሐንስ 18:________

ገጽ  5-6 ጳውሎስ አንድ ምን ይኑራችሁ በማለት ተናገረ? 1 ቆሮንቶስ 1:________

ገጽ 11 ሰዎች ስለ አጉል እምነት እውነቱን ማወቃቸው ምን ውጤት ሊያመጣ ይችላል? ዮሐንስ 8:________

ገጽ 20 አነጋገርህ ምን ሊያሳይ ይችላል? ሉቃስ 6:________

ለልጆች የቀረበ የሥዕል ጥያቄ

ከዚህ መጽሔት ውስጥ እነዚህን ሥዕሎች ማግኘት ትችላለህ? እያንዳንዱ ሥዕል ምን እንደሚያሳይ በራስህ አባባል ግለጽ።

በኢየሱስ የዘር ሐረግ ውስጥ የሚመደበው ማን ነው?

መልሱን ለማግኘት የሚያስችሉህን የሚከተሉትን ፍንጮች ልብ በል። ጥቅሶቹን አውጥተህ አንብብ፤ ከዚያም በተዘጋጀው ክፍት ቦታ ላይ ትክክለኛውን ስም ጻፍ።

2. ․․․․․․․

ፍንጭ:- “የጽድቅ ሰባኪ” ነበርኩ።

2 ጴጥሮስ 2:5ን አንብብ።

3. ․․․․․․․

ፍንጭ:- የኖኅ ልጅ ስሆን ስማችን ሲዘረዘር ምንጊዜም መጀመሪያ ላይ እጠቀሳለሁ።

ዘፍጥረት 6:10ን አንብብ።

4. ․․․․․․․

ፍንጭ:- በእኔ ዘመን ‘ምድር ተከፍላ’ ነበር።

ዘፍጥረት 10:25ን (በ1954 ትርጉም) አንብብ።

▪ መልሱ በገጽ 30 ላይ ይገኛል

በገጽ 31 ላይ ለቀረቡት ጥያቄዎች የተሰጡ መልሶች

1. ጌቴሴማኒ የአትክልት ሥፍራ።

▪ ይሁዳ።

▪ ጴጥሮስ።

2. ኖኅ።—ሉቃስ 3:36

3. ሴም።—ሉቃስ 3:36

4. ፋሌቅ።—ሉቃስ 3:35