መልስህ ምንድን ነው?
መልስህ ምንድን ነው?
የሕልሙ ትርጉም ምንድን ነው?
ዳንኤል 2:25-45 ላይ የሚገኘውን ታሪክ ካነበብክ በኋላ ከታች ያሉትን ጥያቄዎች መልስ።
1. ምስሉ የተሠራው ከየትኞቹ አራት የብረት ዓይነቶች ነው?
․․․․․
․․․․․
․․․․․
․․․․․
2. የብረቶቹ ዓይነቶች የሚያመለክቱት ምንድን ነው?
․․․․․
3. ምስሉ ምን ሆነ?
․․․․․
4. ምስሉን የተካው ምንድን ነው? የሚቆየውስ ለምን ያህል ጊዜ ነው?
․․․․․
․․․․․
ለውይይት:-
ይህ ታሪክ፣ ዳንኤል ትሑት እንደነበር የሚያሳየው እንዴት ነው? አንድን ሥራ በጥሩ ሁኔታ ብታከናውን ወይም አንድ ዓይነት ተሰጥኦ ቢኖርህ ትሑት መሆንህ አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?
ከዚህ እትም
የሚከተሉትን ጥያቄዎች መልስ፤ እንዲሁም የጎደለውን ቁጥር አሟላ።
ገጽ 7 የትዳር ጓደኛሞች ምን ለማድረግ ፈጣን መሆን አለባቸው? ያዕቆብ 1:________
ገጽ 9 የትዳር ጓደኛሞች በምን ነገር ላይ ሊያተኩሩ ይገባል? ፊልጵስዮስ 2:_______
ገጽ 11 አምላክ አገልጋዮቹን ከምን ነገር እንዲርቁ አዟቸዋል? ዘዳግም 18:________
ገጽ 21 አንድ ወጣት ሰሚ ብቻ ሳይሆን አድራጊም ከሆነ ምን ይሆናል? ያዕቆብ 1:________
ለልጆች የቀረበ የሥዕል ጥያቄ
ከዚህ መጽሔት ውስጥ እነዚህን ሥዕሎች ማግኘት ትችላለህ? እያንዳንዱ ሥዕል ምን እንደሚያሳይ በራስህ አባባል ግለጽ።
በኢየሱስ የዘር ሐረግ ውስጥ የሚመደበው ማን ነው?
መልሱን ለማግኘት የሚያስችሉህን የሚከተሉትን ፍንጮች ልብ በል። ጥቅሶቹን አውጥተህ አንብብ፤ ከዚያም በተዘጋጀው ክፍት ቦታ ላይ ትክክለኛውን ስም ጻፍ።
5. ․․․․․
ፍንጭ:- የልጅ ልጄ ሁለተኛው የእስራኤል ንጉሥ ነበር።
1 ሳሙኤል 16:13, 14ን እና 1 ዜና መዋዕል 2:12-15ን አንብብ።
6. ․․․․․
ፍንጭ:- ኢሳይያስ፣ ከእኔ ዘሮች መካከል አንዱ ‘ለሕዝቦች ምልክት ሆኖ እንደሚቆም’ ትንቢት ተናግሯል።
ኢሳይያስ 11:10ን አንብብ።
7. ․․․․․
ፍንጭ:- የሙዚቃ መሣሪያዎችን በመሥራት እታወቅ ነበር።
2 ዜና መዋዕል 7:6ን አንብብ።
▪ መልሶቹ በገጽ 22 ላይ ይገኛሉ
በገጽ 31 ላይ ለቀረቡት ጥያቄዎች የተሰጡ መልሶች
1. ከወርቅ፣ ከብር፣ ከናስ፣ ከብረት።
2. አራት መንግሥታትን።
3. ደቀቀ።
4. የአምላክ መንግሥት፤ ለዘላለም።
5. ኢዮቤድ።—ሉቃስ 3:31, 32
6. እሴይ።—ሉቃስ 3:32
7. ዳዊት።—ሉቃስ 3:31