በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ልጆች ሲያድጉ

ልጆች ሲያድጉ

ልጆች ሲያድጉ

“ሁለታችንም ልጆች እያለን የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ የተባለውን መጽሐፍ በጣም እንወደው ነበር። በአሁኑ ጊዜ፣ ጆሹዋ የሚባል አንድ ዓመት ከአራት ወር የሆነው ልጅ አለን። መጽሐፉ ልጃችንን ለማስተማር ግሩም መሣሪያ ሆኖልናል። ጆሹዋ ገና ሕፃን እያለ እንኳ ቢያንስ 35 የሚሆኑ በመጽሐፉ ላይ የሚገኙ የመጽሐፍ ቅዱስ ባለ ታሪኮችን በስም ያውቃቸው ነበር። ከሚያውቃቸው ቃላት መካከል የእነዚህ ሰዎች ስም ይገኝበታል።”​—ቲሞቲ እና አን

“ትንሹ ልጄ ከታላቁ አስተማሪ ተማር የተባለውን መጽሐፍ እየገለጠ ማየት በጣም ስለሚያስደስተው ገና ከአሁኑ አብዛኞቹን ሥዕሎች ለይቶ ያውቃቸዋል። ይህ ደግሞ በትምህርት ቤትም ሆነ በሌሎች ቦታዎች የሚያጋጥሙትን ችግሮች እንዴት መወጣት እንደሚችል በምክንያት ለማስረዳት ጠቅሞኛል። ይህ መጽሐፍ ከጠበቅኩት በላይ ግሩም ነው!”​—ጄኒፈር

“ወጣቶች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎችና ተግባራዊ መሆን የሚችሉ መልሶች፣ ጥራዝ 2 የተባለው መጽሐፍ የወጣቶችን ሕይወት የሚመለከቱ ጉዳዮችን በሙሉ ይዳስሳል። የአሥራ ዘጠኝ ዓመት ወጣት ስሆን ይህ መጽሐፍ ግብ እንዲኖረኝ፣ ከመጠናናት ጋር በተያያዘ ጥበብ የተንጸባረቀበት ውሳኔ እንዳደርግና ከአምላክ ጋር ያለኝን ዝምድና እንዳሻሽል ረድቶኛል። ወጣት አዋቂ ሳይል ሁሉም ሰው ይህን መጽሐፍ ቢያነብ እንደሚጠቀም ይሰማኛል።”​—ኮርትኒ

የመጽሐፍ ቅዱስ ታሪኮች መማሪያ መጽሐፌ

ከታላቁ አስተማሪ ተማር

ወጣቶች የሚጠይቋቸው ጥያቄዎችና ተግባራዊ መሆን የሚችሉ መልሶች፣ ጥራዝ 2

□ ምልክት ያደረግሁበትን መጽሐፍ(ፎች) ላኩልኝ። ይህን ቅጽ ሞልተው በዚህ መጽሔት ገጽ 5 ላይ ከሚገኙት አድራሻዎች አመቺ ወደሆነው መላክ ይችላሉ።

□ መጽሐፍ ቅዱስ ማጥናት ስለምፈልግ እባካችሁ አነጋግሩኝ።