ረቡዕ ሚያዝያ 12, 2006 ከእኛ ጋር እንዲሰበሰቡ ጋብዘንዎታል
ረቡዕ ሚያዝያ 12, 2006 ከእኛ ጋር እንዲሰበሰቡ ጋብዘንዎታል
ሊታወስ የሚገባው ምሽት
ኢየሱስ ክርስቶስ ከመሞቱ በፊት በነበረው ምሽት የሞቱን መታሰቢያ በዓል አቋቋመ። የወይን ጠጅንና ያልቦካ ቂጣን እንደ ምሳሌ በመጠቀም “ይህን ለመታሰቢያዬ አድርጉት” የሚል መመሪያ ሰጥቷል።—ሉቃስ 22:19
የይሖዋ ምሥክሮች፣ ኢየሱስ ባዘዘው መሠረት በዓመት አንድ ጊዜ በሚያከብሩት በዚህ በዓል ላይ አብረዋቸው እንዲገኙ በአክብሮት ጋብዘዎታል። በዓሉ የሚከበርበትን ቦታ፣ ቀንና ሰዓት ለማወቅ የዚህን ቅጽ ጀርባ መመልከት አሊያም በአካባቢዎ የሚገኙ የይሖዋ ምሥክሮችን መጠየቅ ይችላሉ።