መጠበቂያ ግንብ—የጥናት እትም ግንቦት 2014

ይህ ርዕስ በአገልግሎት ላይ ለሚያጋጥሙን ተፈታታኝ ጥያቄዎች አሳማኝ መልስ ለመስጠት ልንጠቀምባቸው የምንችላቸውን ሦስት ዘዴዎች ያብራራል። ለአምላክ ድርጅት ምንጊዜም ታማኝ መሆናችን በጣም አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

‘የእኔ ምግብ የአምላክን ፈቃድ መፈጸም ነው’

ንጉሥ ዳዊት፣ ሐዋርያው ጳውሎስ እና ኢየሱስ ክርስቶስ የአምላክን ፈቃድ መፈጸም ይፈልጉ ነበር። የምናገለግለው አስቸጋሪ በሆኑ ክልሎች ውስጥ ቢሆን እንኳ ለአገልግሎት ያለንን ቅንዓት ጠብቀን መቀጠል ወይም ቅንዓታችን እንደገና ማቀጣጠል የምንችለው እንዴት ነው?

‘ለእያንዳንዱ ሰው መልስ መስጠት’ ያለብን እንዴት ነው?

አንድ ሰው አስቸጋሪ ጥያቄዎች ሲያቀርብልን አሳማኝ ማስረጃዎችን በማቅረብ ነጥቡን እንዲያመዛዝን መርዳት የምንችለው እንዴት ነው? አሳማኝ መልስ መስጠት የምንችልባቸውን ሦስት መንገዶች እንድታነብብ እንጋብዝሃለን።

በአገልግሎታችሁ ወርቃማውን ሕግ ተግባራዊ አድርጉ

በአገልግሎት ላይ የምናገኘውን እያንዳንዱን ሰው መያዝ የሚገባን እንዴት ነው? ኢየሱስ በማቴዎስ 7:12 ላይ የተናገረው ሐሳብ በስብከት ሥራችን ላይ ምን ተጽዕኖ ያሳድራል?

የሕይወት ታሪክ

የይሖዋ እርዳታ ፈጽሞ አልተለየኝም

ኬነዝ ሊትል፣ ዓይናፋርነትንና በራስ ያለመተማመን ስሜትን ለማሸነፍ ይሖዋ አምላክ የረዳው እንዴት እንደሆነ ተናግሯል። በሕይወቱ ውስጥ ያጋጠሙትን ነገሮች ለማሸነፍ ያደረገውን ጥረት አምላክ የባረከለት እንዴት እንደሆነ አንብብ።

ይሖዋ ነገሮችን በተደራጀ መልክ የሚያከናውን አምላክ ነው

የጥንቶቹ እስራኤላውያንም ሆነ በመጀመሪያው መቶ ዘመን የነበሩት ክርስቲያኖች ታሪክ፣ በዛሬው ጊዜ በምድር ላይ ያሉት የይሖዋ አገልጋዮች እንደሚደራጁ የሚያሳየው እንዴት ነው?

ከይሖዋ ድርጅት ጋር ወደፊት እየተጓዝክ ነው?

የሰይጣን ክፉ ሥርዓት በቅርቡ ይጠፋል። አምላክ በዛሬው ጊዜ በምድር ላይ ከሚጠቀምበት ድርጅት ጋር በታማኝነት ተጣብቀን መቀጠላችን በጣም አስፈላጊ የሆነው ለምንድን ነው?

ከታሪክ ማኅደራችን

‘ገና መሠራት ያለበት ብዙ የመከር ሥራ አለ’

በብራዚል የመጽሐፍ ቅዱስን እውነት የሚያሠራጩ ከ760,000 የሚበልጡ የይሖዋ ምሥክሮች አሉ። የስብከቱ ሥራ በደቡብ አሜሪካ የተጀመረው እንዴት ነው?