በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ዳግመኛ መወለድ ምን ያህል አስፈላጊ ነው?

ዳግመኛ መወለድ ምን ያህል አስፈላጊ ነው?

ዳግመኛ መወለድ​—ምን ያህል አስፈላጊ ነው?

ኢየሱስ ከኒቆዲሞስ ጋር ባደረገው ውይይት ላይ እንደ አዲስ ወይም ዳግመኛ መወለድ በጣም አስፈላጊ መሆኑን ጎላ አድርጎ ገልጿል። ይህን ያደረገው እንዴት ነበር?

ኢየሱስ ከኒቆዲሞስ ጋር ባደረገው ውይይት ላይ ዳግመኛ መወለድ ምን ያህል አስፈላጊ እንደሆነ የገለጸበትን መንገድ ልብ በል። “ማንም ሰው ዳግመኛ ካልተወለደ በቀር የአምላክን መንግሥት ሊያይ አይችልም” ብሏል። (ዮሐንስ 3:3) “በቀር” እና “አይችልም” የሚሉት ቃላት እንደ አዲስ መወለድ ምን ያህል አስፈላጊ መሆኑን የሚያጎሉ ናቸው። ይህን በምሳሌ ለማስረዳት ያህል፣ አንድ ሰው “ፀሐይ ካልወጣች በቀር ብርሃን ሊኖር አይችልም” ቢል ብርሃን እንዲኖር ፀሐይ መውጣቷ የግድ አስፈላጊ መሆኑን መግለጹ ነው። በተመሳሳይም ኢየሱስ የአምላክን መንግሥት ለማየት ዳግመኛ መወለድ የግድ አስፈላጊ መሆኑን መናገሩ ነበር።

ኢየሱስ ስለዚህ ጉዳይ ሊነሳ የሚችለውን ማንኛውንም ዓይነት ጥርጣሬ ለማስወገድ ይመስላል “ዳግመኛ መወለድ አለባችሁ” በማለት በድጋሚ ተናገረ። (ዮሐንስ 3:7) ኢየሱስ ከተናገረው ሐሳብ በግልጽ መረዳት እንደምንችለው ዳግመኛ መወለድ፣ ወደ አምላክ መንግሥት ‘ለመግባት’ የግድ መሟላት ያለበት ብቃት ነው።—ዮሐንስ 3:5

ኢየሱስ ዳግመኛ መወለድ በጣም አስፈላጊ እንደሆነ ስለገለጸ ክርስቲያኖች ስለዚህ ጉዳይ ትክክለኛ ግንዛቤ ለማግኘት ጥረት ማድረግ ይኖርባቸዋል። ለምሳሌ፣ ‘እንደ አዲስ መወለድ በአንድ ክርስቲያን ምርጫ ላይ የተመካ ጉዳይ ነው?’ የሚለውን ጥያቄ እንመርምር።

[በገጽ 5 ላይ የሚገኝ የተቀነጨበ ሐሳብ]

“ፀሐይ ካልወጣች በቀር ብርሃን ሊኖር አይችልም”