በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

“ልብህን ጠብቅ!”

“ልብህን ጠብቅ!”

“ልብህን ጠብቅ!”

የይሖዋ ምሥክሮች የአውራጃ ስብሰባ

የዓርብ ዕለት ጭብጥ

‘ይሖዋ ልብን ያያል’​—1 ሳሙኤል 16:7

የቅዳሜ ዕለት ጭብጥ

“አንደበት የሚናገረው በልብ ውስጥ የሞላውን ነው”​—ማቴዎስ 12:34

የእሁድ ዕለት ጭብጥ

‘ይሖዋን በፍጹም ልብ አገልግለው’​—1 ዜና መዋዕል 28:9

ልብ የሚለው ቃል በመጽሐፍ ቅዱስ ውስጥ አንድ ሺህ ጊዜ ያህል ይገኛል። በአብዛኞቹ ቦታዎች ቃሉ የተሠራበት ቃል በቃል ሳይሆን ምሳሌያዊ በሆነ መንገድ ነው። ታዲያ ምሳሌያዊው ልብ ምን ያመለክታል? ምሳሌያዊው ልብ የአንድን ሰው ውስጣዊ ማንነት ይኸውም ሐሳቡን፣ ስሜቱንና ፍላጎቱን ሊያመለክት ይችላል።

ምሳሌያዊውን ልባችንን መጠበቅ ያለብን ለምንድን ነው? ንጉሥ ሰለሞን በአምላክ መንፈስ መሪነት እንዲህ ሲል ጽፏል፦ “ከሁሉም በላይ ልብህን ጠብቅ፤ የሕይወት ምንጭ ነውና።” (ምሳሌ 4:23) ምሳሌያዊው ልባችን ያለበት ሁኔታ በአሁኑ ጊዜ በምንመራው ሕይወትም ሆነ በወደፊቱ ሕይወታችን ላይ ተጽዕኖ ያሳድራል። እንዲህ የምንለው ለምንድን ነው? አምላክ የሚያየው ልባችንን ስለሆነ ነው። (1 ሳሙኤል 16:7) አምላክ ለእኛ ያለው አመለካከት የሚወሰነው በውስጣዊ ማንነታችን ይኸውም ‘በተሰወረው የልብ ሰው’ ነው።​—1 ጴጥሮስ 3:4

ልባችንን መጠበቅ የምንችለው እንዴት ነው? የዚህ ጥያቄ መልስ የይሖዋ ምሥክሮች በሚያደርጉት የአውራጃ ስብሰባ ላይ በጥልቀት ይብራራል፤ በዓለም ዙሪያ የሚደረገው ይህ ስብሰባ በዚህ ወር ይጀምራል። በሦስቱም ቀናት በስብሰባው ላይ እንዲገኙ በአክብሮት ተጋብዘዋል። * በስብሰባው ላይ የሚቀርበው ትምህርት የይሖዋ አምላክን ልብ ደስ በሚያሰኝ መንገድ ሕይወትዎን ለመምራት ያስችልዎታል።​—ምሳሌ 27:11

[የግርጌ ማስታወሻ]

^ አን.11 የአውራጃ ስብሰባው በአቅራቢያዎ የሚደረግበትን ቦታ ለማወቅ www.pr418.com የሚለውን ድረ ገጽ ይጎብኙ። በተጨማሪም በአካባቢዎ ያሉትን የይሖዋ ምሥክሮች ማነጋገር አሊያም ለዚህ መጽሔት አዘጋጆች መጻፍ ይችላሉ።

[በገጽ 32 ላይ የሚገኝ የሥዕል ምንጭ]

Photo on right: Aus dem Fundus der MÜNCHNER OLYMPIAPARK GMBH, München