በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

መዝሙር 52

ራስን ለአምላክ መወሰን

ራስን ለአምላክ መወሰን

(ዕብራውያን 10:7, 9)

  1. 1. ይሖዋ ስለፈጠረ

    ግዙፉን ጽንፋለም፣

    ሰማይ፣ ምድር ንብረቱ ነው፤

    የሱ ናቸው ሁሉም።

    ሕይወት፣ እስትንፋስ ለሰጠን፣

    ይድረስ ምስጋናችን።

    ሊወደስ ሊመለክ ይገባል፤

    ሁሉን በነፃ ሰጥቷል።

  2. 2. ጽድቅን ሊፈጽም ኢየሱስ

    በውኃ ተጠምቋል።

    በፈቃደኝነት ራሱን

    ለአምላክ አቅርቧል።

    ከዮርዳኖስ ውኃ ወጥቶ፣

    በመንፈስ ሲቀባ፤

    ‘ፈቃድህን ማድረግ እሻለሁ’

    ብሎ ላምላክ ቃል ገባ።

  3. 3. ይሖዋ ልናወድስህ

    በፊትህ ቀርበናል።

    ከልብ ራሳችንን ክደን

    ላንተ ወስነናል።

    በውድ ዋጋ ተገዝተናል፤

    የልጅህ ደም ፈሷል።

    ብንኖር፣ ብንሞት ያንተው ነን፤

    አበቃ የራስ መሆን።

(በተጨማሪም ማቴ. 16:24⁠ን፣ ማር. 8:34⁠ን እና ሉቃስ 9:23⁠ን ተመልከት።)