በቀጥታ ወደ ዋናው ጉዳይ ግባ

በቀጥታ ወደ ርዕስ ማውጫው ሂድ

ክርስቲያናዊ ሕይወት

ይሖዋ መንፈሳቸው የተደቆሰባቸውን ያድናል

ይሖዋ መንፈሳቸው የተደቆሰባቸውን ያድናል

ሁሉም ሰው አልፎ አልፎ ያዝናል። የሐዘን ስሜት የመንፈሳዊ ድክመት ምልክት አይደለም። ይሖዋም እንኳ ሳይቀር ሐዘን የተሰማው ጊዜ እንዳለ ገልጿል። (ዘፍ 6:5, 6) ይሁንና በተደጋጋሚ ወይም ሁልጊዜ በሐዘን ስሜት ብንዋጥስ?

ይሖዋ እንዲረዳችሁ ጸልዩ። ይሖዋ አእምሯዊና ስሜታዊ ጤንነታችን በጣም ያሳስበዋል። ስንደሰትና ስናዝን ያስተውላል። በአስተሳሰባችንና በስሜታችን ላይ ተጽዕኖ የሚያሳድሩትን ነገሮች ይረዳል። (መዝ 7:9ለ) ከሁሉ በላይ ደግሞ፣ ይሖዋ በጣም ያስብልናል፤ እንዲሁም ሐዘንን አልፎ ተርፎም የመንፈስ ጭንቀትን ለመቋቋም ይረዳናል።—መዝ 34:18

የአእምሮ ጤንነታችሁን ተንከባከቡ። አሉታዊ ስሜቶች ደስታችንንም ሆነ አምልኳችንን ሊነኩ ይችላሉ። በዚህም የተነሳ ልባችንን ማለትም መላውን ውስጣዊ ማንነታችንን መጠበቅ ይኖርብናል።—ምሳሌ 4:23

ወንድሞቻችን ሰላማቸውን ጠብቀው እየኖሩ ያሉት እንዴት ነው?—የመንፈስ ጭንቀት ቢያጋጥማቸውም የሚለውን ቪዲዮ ተመልከት፤ ከዚያም የሚከተሉትን ጥያቄዎች ለመመለስ ሞክር፦

  • ኒኪ ከመንፈስ ጭንቀት ጋር የምታደርገውን ትግል ለማሸነፍ ምን ተግባራዊ እርምጃዎችን ወስዳለች?

  • ኒኪ የሕክምና እርዳታ እንደሚያስፈልጋት የተሰማት ለምንድን ነው?—ማቴ 9:12

  • ኒኪ በይሖዋ እርዳታ እንደምትታመን ያሳየችው በየትኞቹ መንገዶች ነው?